የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና አሰጣጥ ሂደትን ዛሬ ሐምሌ 21/2015 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው ተመልክተዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከ‹‹AMU-IUC›› ፕሮጀክት V ጋር በመተባበር ‹‹Evidence-based Training for Model Farmers and Stakeholders on Solutions to Challenges of Enset Production and Livestock Feed Security in Gamo Zone, Southern Ethiopia›› በሚል ርእስ ከጋሞ ዞን ሰባት ወረዳዎች ለመጡ አርሶ አደሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች ከሐምሌ 05-08/2015 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር ተመድበው የመጡ የመጀመሪያ ዙር የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች፣ ፈታኞች፣ የፈተና አስፈጻሚዎችና አስተባባሪዎች ቅበላና አጠቃላይ የፈተና አሰጣጥ ገለጻ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በስድስቱም ካምፓሶቹ 11,773 ወንድ እና 12,354 ሴት በድምሩ 24,127 ተማሪዎች የተቀበለ ሲሆን በትምህርት ሚኒስቴር መርሃ ግብር መሠረት ፈተናውን ከሐምሌ 19/2015 ዓ/ም ጀምሮ የሚወስዱ ይሆናል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከራእይ ፕሮጀክት እና ከአርባ ምንጭ ከተማ ሴቶችና ሕፃናት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከውሃ ምንጭ ቀበሌ ሃይላንድ መንደር ለተወጣጡ በእንጨት ለቀማ ለሚተዳደሩና በፕሮጀክቱ ለታቀፉ 91 ሴቶች ሐምሌ 7/2015 ዓ/ም የሕይወት ክሂሎትና ሥራ ፈጠራ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አቶ ፍሬው ዳንኤል ከአባታቸው ከአቶ ዳንኤል ሻሌ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አማረች ጸላ በቀድሞው ጋሞ ጎፋ አውራጃ አርባ ምንጭ ወረዳ ቆላ ሼሌ ቀበሌ በ1976 ዓ/ም ተወለዱ፡፡