በአዲሱ የፌዴራል መንግሥት መዋቅራዊ አደረጃጀት ለውጥ መሠረት የአስተዳደር ሠራተኞችን ድልደላ ለመፈጸም የየሥራ ክፍሉ ተወካይ ሠራተኞች በተገኙበት ሰኔ 26/2015 ዓ/ም የድልደላና ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች የሠራተኛ ተወካይ ምርጫ ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ በ“Geography and Environmental Studies” ትምህርት ክፍል በ“Disaster Risk Management” ትምህርት ፕሮግራም ላላፉት 5 ዓመታት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር መኩሪያ ጉዬ የምርምር ሥራውን ሰኔ 24/2015 ዓ/ም የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርቦ ተገምግሟል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ በእንግሊዝኛ ቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ ት/ክፍል ‹‹English Language Teaching /ELT/›› የትምህርት ፕሮግራም ላለፉት 5 ዓመታት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር አዲሱ አዳሙ የምርምር ሥራውን ሰኔ 23/2015 ዓ/ም የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርቧል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ በሥጋ ቁጥጥርና አያያዝ ዙሪያ በተቋቋመ ፕሮጀክት አማካኝነት ‹‹Enhancing Slaughter House Service›› በሚል ርዕስ ከጋሞ ዞን ከተመረጡ የቄራ አገልግሎት ማዕከላት ለመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ከሰኔ 21-23/2015 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በሥራና ክሂሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ‹‹ማሠልጠን፣ ማብቃትና መሸለም›› በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በ‹‹ብሩህ ኢትዮጵያ 2015 የሥራ ፈጠራ ሃሳብ ውድድር›› ላይ የተሳተፉ ተማሪ ሰርካለም ደሳለኝ እና አልአዛር ቅጣው አሸነፉ፡፡ ከውድድር መልስም  ሰኔ 20/2015 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው የእንኳን ደስ አላችሁ አቀባበል ተደርጓል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ