- Details
በ2015 የትምህርት ዘመን አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቅበላ ቀን የካቲት 22/2015 ዓ/ም፣ የምዝገባ ቀን የካቲት 23 እና 24 ቀን 2015 ዓ.ም ፣ ትምህርት የሚጀመርበት ቀን የካቲት 27 ቀን 2015 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል፡፡
ስለሆነም ተማሪዎች በተጠቀሰው ቀን ወደ ዩኒቨርሲቲው በሚትመጡበት ጊዜ፡-
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት በጨንቻ ዙሪያ ወረዳ በሚገኘው ሻማ ጎማ፣ ቀርጴ እና በሌ ቀርጴ መንደሮች ላይ በ1.9 ሚሊየን ብር ያስገነባውን የሻማ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የካቲት 12/2015 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ከፕሮጀክት ሥራው 400 ሺህ ብር ወጪ የተሸፈነው ማኅበረሰቡ በጉልበቱ ባበረከተው አስተዋፅዖ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ1.9 ሚልየን ብር ያስገነባውን የሻማ ቀበሌ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አስመረቀ
- Details
Arba Minch University in collaboration with Deutsche Gesellschaft für Internationale Zusammenarbeit (GIZ), the main German Development Agency, hosted Inception and Promotion Workshop on “Women in Agriculture and Rural Livelihoods” on February 14, 2023. Click here to see more pictures.
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከ‹‹GIZ›› ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ‹‹Women in Agriculture and Rural Livelihoods›› በሚል ርዕስ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎችና መምህራን በተገኙበት የካቲት 6/2015 ዓ/ም ወርክሾፕ አካሂዷል፡፡ በወርክሾፑ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
ተማሪ አየለ አካሉ ከእናቱ ወ/ሮ ሙሉነሽ መርሻ እና ከአባቱ ከአቶ አካሉ ወልደኪዳን በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ ሰላ ድንጋይ ፍላገነት ቀበሌ በ1991 ዓ/ም ተወለደ፡፡ ተማሪ አየለ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በወረዳው እምቧይ ባድ ሙሉ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርቱን በሳሲት አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም የመሰናዶ ትምህርቱን በሰላ ድንጋይ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት ተከታትሏል፡፡