አቶ ሙሉነህ መንገሻ ከአባታቸው ከአቶ መንገሻ ቃንኤ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ዓለሚቱ በላቸው በቀድሞ በሰሜን ኦሞ ዞን በጋሞ አውራጃ በቁጫ ወረዳ መስከረም 12/1958 ዓ.ም ተወለዱ፡፡

የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀድሞ በጎፋ ወረዳ በገልጣ ከተማ  1- 6 ክፍል በገሪማ 1 ደረጃ ት/ቤት፣ ከ7- 8 ክፍል በአርባ ምንጭ ከተማ በኩልፎ ሙሉ 1 ደረጃ ት/ቤት እና ከ9- 10 ክፍል  የ2 ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኮሚዩኒቲ  2 ደረጃ  ት/ቤት አጠናቀዋል፡፡

ወ/ሮ መርታን መርዕድ ከአባታቸው ከአቶ መርዕድ ዱለቻ እና ከእናታቸው ወ/ሮ አየለች ቡሩኮ በአርባ ምንጭ ከተማ ወዜ ቀበሌ ጳጉሜ 3/1978 ዓ.ም ተወለዱ፡፡

 የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን (ከ1 - 6) ክፍል በዓለም 1 ደረጃ ት/ቤት፣ የ7እና 8 ክፍል ትምህርታቸውን በኩራዝ መለስተኛ 2 ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም የ2 ደረጃ ትምህርታቸውን በጂንካ አጠቃላይ 2 ደረጃ ት/ቤት ያጠናቀቁ ሲሆን በ1996 ዓ.ም ሚዛን ቴፒ ግብርና ኮሌጅ በመግባት በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ትምህርት በ1998 ዓ/ም በዲፕሎማ ተመርቀዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ለሁሉም ካምፓሶች ለተመራቂ ተማሪዎች ወደ ሥራ ዓለም ሲገቡ ሊገጥሟቸው የሚችሉ የብልሹ አሠራር ችግሮችን የመከላከል ግንዛቤን ለማዳበር ከመስከረም 5-6/2015 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያና በ2ኛ ዲግሪ መርሃ ግብሮች በመደበኛ፣ በማታ፣ በክረምት፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይና ርቀት መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ የ35ኛው ባች 2ኛ ዙር  1,200 ተማሪዎችን መስከረም 12/2015 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 84ቱ በሕክምና ዶክትሬት ዲግሪ የተመረቁ ሲሆን ከአጠቃላይ ምሩቃንም 387ቱ ሴቶች ናቸው፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ