የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት የማኅበረሰብ ጉድኝት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን/The United Nations High Commissioner for Refugees (UNHCR) ቢሮ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በተፈናቃይ ሰዎች የሕግ ጥበቃ፣ በሴቶችና ሕፃናት መብት ጥበቃ፣ በንብረት ሕግ እንዲሁም በካምፓላ ስምምነት ዙሪያ በአሌ ልዩ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ 17 ቀበሌያት ለተወጣጡ የማኅበራዊ፣ የወረዳና የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች፣ መርማሪ ፖሊሶች፣ የፍትሕ ቢሮ ዐቃቤያን ሕግ እንዲሁም ከሴቶችና ሕፃናት እና ከልዩ ወረዳው ምክር ቤት ለተወጣጡ 30 ሠልጣኞች ከነሐሴ 30 - ጳጉሜ 1/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምኅንድስና እና ሒሳብ /Science, Technology, Engineering & Maths – STEM/ ማዕከል ከዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰብ ጉድኝትና ከተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክቶሬቶች እንዲሁም ከ ‹‹STEM Power›› መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር ከጋሞ፣ ጎፋና ኮንሶ ዞኖች እና ከደራሼ፣ ባስኬቶ፣ ቡርጂና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ 291 ከ7ኛ- 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ፣ ፊዚክስ፣ ሒሣብ፣ ኤሌክትሮኒክስና ICT ትምህርቶች ከሐምሌ 15 - ነሐሴ 28/2014 ዓ/ም ሲሰጥ የቆየውን የሥልጠና መርሃ ግብር አጠናቋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የውሃ ሀብትና መስኖ ምኅንድስና እና የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሜካኒካል ምኅንድስና ፋከልቲዎች ነሐሴ 27/2014 ዓ/ም የ3ኛ ዲግሪ ትምህርት መርሃ ግብር የሥርዓተ ትምህርት የውጭ ግምገማ አካሂደዋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ