የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ከተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን/The United Nations High Commissioner for Refugees (UNHCR) ጋር ባደረገው ስምምነት ኮንሶ፣ ደራሼ እና አሌ አካባቢዎች በግጭት ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎችና መብታቸውን ለማስከበር አቅም ለሚያንሳቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ነፃ የሕግ ድጋፍ ለማድረግ ከመጋቢት 2014 ዓ/ም ጀምሮ ለአንድ ዓመት የሚቆይ ‹‹UNHCR-Arba Minch University Project›› የጋራ ፕሮጀክት አስጀምሯል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተከናወኑ የምርምር ሥራዎች ላይ ተመሥርቶ በጫሞ ሐይቅ ተፋሰስ ሥር በሚገኙ 10 ወረዳዎች ዘላቂ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ለማከናወን በጀርመን ልማት ባንክ፣ በኢትዮጵያ መንግሥት፣ በGIZ እና በማኅበረሰብ ተሳትፎ በሚሸፈን ከ1.8 ቢሊየን ብር በላይ በጀት የሚከናወንና ለ5 ዓመታት የሚቆይ ፕሮጀክት /Sustainable Land Management Project/ ይፋ ሆኗል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አቶ ዮናስ አስፋው ከአባታቸው ከአቶ አስፋው ማዳ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አስካለች ቦርቾ በቀድሞው ጋሞ ጎፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ወዜ ቀበሌ በ1981 ዓ/ም ተወለዱ፡፡

የዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከክርስቲያን ኤይድ/Christian Aid/ ጋር በመተባበር ከተለያዩ ጥቃቶች ለመከላከልና የተሞከሩ ወይም የተፈጸሙ ጥቃቶችን ለማስተካከል የሚወሰዱ እርምጃዎችን የሚያሳይ ፖሊሲ ዙሪያ ለዩኒቨርሲቲው ዳይሬክተሮችና ሳይንቲፊክ ዳይሬክተሮች ከነሐሴ 19-20/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹International Youth Fellowship›› ከተባለ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በአእምሮ ቀረጻ(Mind Set) ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ሐምሌ 30/2014 ዓ/ም የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ 
ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ