አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹International Youth Fellowship›› ከተባለ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በአእምሮ ቀረጻ(Mind Set) ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ሐምሌ 30/2014 ዓ/ም የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ 
ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተመራቂ ተማሪዎች በካምባ፣ ገረሴ፣ ቆላ ሼሌ፣ ብርብር፣ ዋጂፎ፣ ቦዲቲና አረካ ጤና ጣቢያዎች በቡድን ሥልጠና ፕሮግራም የቆዩበትን የመስክ ሪፖርት የኮሌጁ ገምጋሚ መምህራን በተገኙበት ነሐሴ 16/2014 ዓ/ም አቅርበዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በዩኒቨርሲቲው የሥልጣን ዘመናቸውን ያጠናቀቁትን የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር የሚተኩ አመራሮችን አወዳድሮ ለመመደብ የእጩ መልማይና የምልመላ ኮሚቴ አባላት
ነሐሴ 16/2014 ዓ/ም ተመርጠዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2014 የትምህርት ዘመን በመደበኛ መርሃ-ግብር ለተመረቁ ተማሪዎች ወንድ 3.5 እና ከዚያ በላይ፣ ሴት 3.25 እና ከዚያ በላይ ውጤት ላስመዘገቡ በ2015 የትምህርት ዘመን ነፃ የ2ኛ ዲግሪ ትምህርት ዕድል ለ18 ተማሪዎች (AMIT 2፣ AWTI 2፣ CBE 2, CSSH 2, CMHS 2, CAS 2, CNS 2, School of Law 1, school of PBS 1, Sawula campus 2)  አወዳደሮ ለመስጠት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የዕድሉ ተጠቃሚ ለመሆን የሚትፈልጉ የ2014 ተመራቂ ተማሪዎች ( መስከረም 29/30 እና ሰኔ 25/26 2014 ዓ.ም የተመረቃችሁ) ከነሐሴ 18-27/2014 ዓ/ም ድረስ ባሉት የሥራ ቀናት እንድትመዘገቡ እየገለጽን፡-

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ/ICT/ ዳይሬክቶሬት ከኮምፒውቲንግና ሶፍትዌር እና ከኤሌክትሪካልና ኮሚፒውተር ምኅንድስና ፋከልቲዎች ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የዲጂታል ሊትረሲ የሥልጠናና ሰርተፊኬሽን ወርክሾፕ ከነሐሴ 11-14/2014 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ