በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ምርምር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አዘጋጅነት በሀገሪቱ እየጨመረ የመጣውን የዋጋ ግሽበት አስመልክቶ በተሠራ ጥናታዊ ጽሑፍ ላይ ለት/ክፍሉ መምህራንና ለባለ ድርሻ አካላት ሰኔ 3/2014 ዓ/ም ትምህርታዊ ገለጻ ተሰጥቷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት ት/ክፍል ከጋሞ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ጋር በመተባበር በወጣቶች ሰብእና ግንባታ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በአመራር ክሂሎት ዙሪያ በጨንቻ ወረዳ ለሚገኙ ወጣት አደረጃጀቶች፣ ኢንተርፕራይዞችና ሥራ ፈላጊ ወጣቶች ሰኔ 3/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

በአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት 20ኛው ዓለም አቀፍ ‹‹ዘላቂ የውሃ ሀብት ልማት›› የምርምር ሲምፖዚየም ከሰኔ 3-4/2014 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡

አርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 20ኛው ‹‹የውሃ ሀብቶች ለዘላቂ ልማት›› ዓለም አቀፍ የምርምር ሲምፖዚየም ላይ እንዲታደሙ ከተጋበዙ ከተለያዩ ተቋማት የመጡ አካላት ጋር ሰኔ 1/2014 ዓ/ም በትብብር ለመሥራት የሚያስችል ውይይት አካሂዷል፡፡

ስለድንበር ተሻጋሪ ወንዞችና የውሃ ሀብት ግንዛቤ ለመፍጠር በቅንጅት ለመሥራት የሚያስችል የውሃ፣ የውሃ ዲፕሎማሲና ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መማክርት ፎረም ሰኔ 2/2014 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በይፋ ተመሥርቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ