የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የ3ኛ ዲግሪ ምሩቃን በ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራም መማር ለሚፈልጉ በትምህርት ሂደቱ ዙሪያ ግንቦት 10/2014 ዓ/ም የልምድ ልውውጥ አካሂደዋል፡፡ 

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ግምገማና ትግበራ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በሁሉም ካምፓስ በሚገኙ የቅድመ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞች የግለ ግምገማ ሰነድ አዘገጃጀት ዙሪያ ግንቦት 10/2014 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ት/ቤት የሰብዓዊ መብት ክበብ ለማቋቋምና በጋራ ለመሥራት ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ማዕከል ጋር በየዓመቱ እየታደሰ ለ3 ዓመት የሚቆይ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ግንቦት 10/2014 ዓ/ም ተፈራርሟል፡፡ በዕለቱ የሰብዓዊ መብት ኮሚቴዎችም ተመርጠዋል፡፡ 

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ት/ቤት ከተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር የምሥራቅ አፍሪካ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት (United Nations Office of the High Commissioner, East African Branch) እና ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ማዕከል ጋር በመተባበር ከዩኒቨርሲቲውና እና በከተማው ከሚገኙ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተወጣጡ 84 ተማሪዎች እንዲሁም ለመምህራንና ለዩኒቨርሲቲው ነፃ የሕግ ድጋፍ መስጫ ማዕከላት ሠራተኞች በመሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ ከግንቦት 8-10/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡