አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከግብርና ሳይንስ፣ ከተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ እና ከሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጆች ጋር በመተባበር 8ኛውን ሳይንስ ለዘላቂ ልማት ዓውደ ጥናት ከመጋቢት 30 - ሚያዝያ 01/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ በዓውደ ጥናቱ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተወጣጡ በግብርና፣ ጤና እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፎች የተዘጋጁ 58 ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ሴቶች በሚደርስባቸው ጾታዊ ትንኮሳ፣ አድልኦ፣ የሥራ ጫና፣ ከወንዶች እኩል አለመታየትና በሌሎችም ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ መጋቢት 21/2014 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹The Economics of Land Degradation Initiative››፣ ‹‹GRÓ, Land Restoration Training Program›› ከተሰኙ መቀመጫቸውን ጀርመንና አይስላንድ ካደረጉ ተቋማትና GIZ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ‹‹Integrated Approaches for Land Restoration through Sustainable Land and Aquatic Management›› በሚል ርዕስ ከጫሞ ተፋሰስ 10 ወረዳዎች ለተወጣጡ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች ከመጋቢት 19-23/2014 ዓ/ም ለ5 ቀናት የቆየ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ 

የሴቶችን አቅም ከማጎልበት፣ ከሕግና ከሥልጠና ድጋፎች አንጻር አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በማኅበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ ለሠራቸው ሥራዎች የጨንቻ ዙሪያ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት መጋቢት 19/2014 ዓ/ም የዕውቅና ምስክር ወረቀት አበርክቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ