አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፌዴራል ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት/FDRE Construction Management Institute/ ጋር በመተባባር “Building Information Management/BIM”በሚል ርዕስ ለዩኒቨርሲቲው ቴክኖሎጂ እና ለውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች መምህራን፣ ለዩኒቨርሲቲው ግንባታ ፕሮጀክትና ለፋሲሊቲ አስተዳደር ዘርፍ ባለሙያዎች ከጥር 13 - 30/2016 ዓ.ም ድረስ ስለግንባታ ሞዴልንግ ቴክኖሎጂ ሥልጠና እየተሰጠ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ፣ ነጭ ሳር፣ ኩልፎና ዓባያ ካምፓሶች ለሚገኙ የመጀመሪያ ዓመት ፍሬሽ ማን ኮርስ የጨረሱ ተማሪዎች በፋከልቲና ዲፓርትመንት መረጣ ዙሪያ ከጥር 09-10/2016 ዓ/ም ገለጻ ተደርጓል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

United States Agency for International Development, USAID-Ethiopia, and Feed the Future -Ethiopia Transforming Agriculture visited Arba Minch University’s research and community engagement and job-creation and tech-transfer initiatives on Enset Processing and productivity from January 21-22, 2024. Click here to see more photos.

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የመስክ ምልከታ በማድረግ እና ከተማሪ ተወካዮች የተነሱ ጥያቄዎችን አስመልክቶ በትኩረት ሊሠሩ በሚገቡ ጉዳዮች ዙሪያ ለዩኒቨርሲቲው ካውንስል ጥር 13/2016 ዓ/ም ግብረ መልስ ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የሥነ-ትምህርትና ሥነ-ባህሪ ሳይንስ ት/ቤት የባህሪ ማሻሻያ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከ “International Youth Fellowship” ጋር በመተባበር በአዕምሮ ውቅር (mindset) ዙሪያ ከኮሪያ በመጡ አሠልጣኞች ለጫሞ፣ ለዋናው ግቢ 2 ዓመትና ከዚያ በላይ ለሆኑ የዩኒቨርሲቲው መደበኛ፣ ኢ-መደበኛና ለሁሉም ሪሚዲያል ተማሪዎች፣ ለባይራ አዳሪ 2 ደ/ት/ቤት ተማሪዎች እና ለአርባ ምንጭ ከተማ መምህራን ከጥር 17-18/2016 ዓ.ም በዋናው ግቢ በሚገኝ አዳራሽ ሥልጠና የሚሰጥ ይሆናል፡፡