አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹The Economics of Land Degradation Initiative››፣ ‹‹GRÓ, Land Restoration Training Program›› ከተሰኙ መቀመጫቸውን ጀርመንና አይስላንድ ካደረጉ ተቋማትና GIZ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ‹‹Integrated Approaches for Land Restoration through Sustainable Land and Aquatic Management›› በሚል ርዕስ ከጫሞ ተፋሰስ 10 ወረዳዎች ለተወጣጡ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች ከመጋቢት 19-23/2014 ዓ/ም ለ5 ቀናት የቆየ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ 

የሴቶችን አቅም ከማጎልበት፣ ከሕግና ከሥልጠና ድጋፎች አንጻር አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በማኅበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ ለሠራቸው ሥራዎች የጨንቻ ዙሪያ ወረዳ ሕዝብ ምክር ቤት መጋቢት 19/2014 ዓ/ም የዕውቅና ምስክር ወረቀት አበርክቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥነ-ትምህርትና ሥነ-ባህሪ ሳይንስ ት/ቤት ‹‹Enhancing Community Development in Malo Koza Woreda›› በሚል ርዕስ በመሎ ኮዛ ወረዳ ላሃ ከተማ መጋቢት 17/2014 ዓ.ም የምርምር ውጤት ማረጋገጫ ወርክ ሾፕ አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት በዓለም ለ111ኛ በሀገራችን ለ46ኛ ጊዜ የተከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ‹‹እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ›› በሚል መሪ ቃል መጋቢት 15/2014 ዓ/ም የካምፓሱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር፣ ሴት የአስተዳደር ሠራተኞችና ሴት ተማሪዎች በተገኙበት በሳውላ ካምፓስ አክብሯል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ