የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትኩረት የሚሹ የቆላማ አካባቢ በሽታዎች ምርምርና ሥልጠና ማዕከል ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ‹‹Quality of Leishmanisis Case Management in SNNPR›› በሚል ርዕስ ግማሽ ሚሊየን ብር የተመደበለት የዳሰሳ ጥናት ለማከናወን እየተዘጋጁ ሲሆን በጥናቱ ለሚሳተፉ መረጃ ሰብሳቢዎችና ሱፐርቫይዘሮች መጋቢት 01/2013 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት በዓለም ለ111ኛ በሀገራችን ለ46ኛ ጊዜ የተከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ‹‹እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ›› በሚል መሪ ቃል መጋቢት 01/2014 ዓ/ም የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣መምህራን፣ ሴት የአስተዳደር ሠራተኞችና ሴት ተማሪዎች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አክብሯል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ከኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ጋር በመተባበር ለፍ/ቤቱ ዳኞች፣ ሬጂስትራሮችና ዐቃቤያን ሕግ የወንጀል፣ የውልና ከውል ውጪ ኃላፊነቶች ሕግ ላይ ከመጋቢት 01/2014 ዓ/ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት የሚቆይ ሥልጠና እየሰጠ ነው፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ከ9 ሺህ በላይ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችና ተማሪዎች የኮሮና ቫይረስ ክትባት ከነገ የካቲት 30/2014 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 3 ቀናት እንደሚሰጥ ተገለጸ፡፡ በክትባቱ አሰጣጥና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል ዛሬ የካቲት 29/2014 ዓ/ም መክሯል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ