የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ መንግሥት ፍትሕ ቢሮ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ጋር በመተባበር በፍትሐብሔር አሠራር ማኑዋል፣ በግንባታ ውሎች፣ በፍርድ ቤት ሥልጣን፣ በክስ አቀራረብና መስማት ሂደት እና በመጥሪያ አደራረስ ላይ በክልሉ ከሚገኙ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ ዐቃቤያን ሕግ ከጥር 28-29/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ዲግሪ ነባር የክረምት መርሃ-ግብር ተማሪዎች ከየካቲት 14-19/2014 ዓ.ም ድረስ ቲቶሪያል የሚሰጥ ስለሆነ በየካምፓሶቻችሁ ተገኝታችሁ ገለጻውን እንድትከታተሉ ዩኒቨርሲቲው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሕወሓት ወራሪ ኃይል ከፍተኛ ጉዳት ላጋጠመው ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ማስተማር ሥራ የሚውሉ ላፕቶፖች፣ ወረቀቶች፣ ካኪ ፖስታዎች፣ እስክሪብቶዎች፣ ቾክ፣ የቢሮና የተማሪ ወንበሮች፣ የማስተማሪያ ጠረጴዛዎች፣ ለተማሪ የምግብ አገልግሎት የሚውሉ የካፍቴሪያ ዕቃዎች፣ የውሃ ማጠራቀሚያ ፕላስቲክ ጋኖች፣ የእንጀራ ምጣዶች፣ የፍራሽ፣ የዕቃ ማመላለሻ ጋሪዎችና የመሳሰሉ ቁሳቁሶችን ጥር 21 እና 22/2014 ዓ.ም በወልድያ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት ድጋፍ አድርጓል፡፡ የቁሳቁስ ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን 2.5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ተማሪ ጽጌሬዳ ግርማይ ከአባቷ ከአቶ ግርማይ ገ/መድኅን እና ከእናቷ ከወ/ሮ ያበሻ ያዘዘው ወልቃይት ወረዳ አዲ ረመጽ ከተማ በ1993 ዓ/ም ተወለደች፡፡

ተማሪ ፅጌሬዳ ግርማይ የመሰናዶ ትምህርቷን በወልቃይት ጌታቸው አዘናው 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትላለች፡፡  ፎቶዎችን ለማየት

በዩኒቨርሲቲ ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ከ13 የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ለተወጣጡ መምህራን ‹‹Solid work››፣ ‹‹Arc cad›› እና ‹‹Auto cad›› በተሰኙ የኮንስትራክሽን ሶፍትዌሮች ዙሪያ ከጥር 16-20/2014 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡