- Details
የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ መንግሥት ፍትሕ ቢሮ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ጋር በመተባበር በፍትሐብሔር አሠራር ማኑዋል፣ በግንባታ ውሎች፣ በፍርድ ቤት ሥልጣን፣ በክስ አቀራረብና መስማት ሂደት እና በመጥሪያ አደራረስ ላይ በክልሉ ከሚገኙ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ ዐቃቤያን ሕግ ከጥር 28-29/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
Read more: በደቡብ ክልል ከሚገኙ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ ዐቃቤያን ሕግ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ዲግሪ ነባር የክረምት መርሃ-ግብር ተማሪዎች ከየካቲት 14-19/2014 ዓ.ም ድረስ ቲቶሪያል የሚሰጥ ስለሆነ በየካምፓሶቻችሁ ተገኝታችሁ ገለጻውን እንድትከታተሉ ዩኒቨርሲቲው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
Read more: ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ነባር የክረምት መርሃ -ግብር ተማሪዎች በሙሉ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሕወሓት ወራሪ ኃይል ከፍተኛ ጉዳት ላጋጠመው ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ማስተማር ሥራ የሚውሉ ላፕቶፖች፣ ወረቀቶች፣ ካኪ ፖስታዎች፣ እስክሪብቶዎች፣ ቾክ፣ የቢሮና የተማሪ ወንበሮች፣ የማስተማሪያ ጠረጴዛዎች፣ ለተማሪ የምግብ አገልግሎት የሚውሉ የካፍቴሪያ ዕቃዎች፣ የውሃ ማጠራቀሚያ ፕላስቲክ ጋኖች፣ የእንጀራ ምጣዶች፣ የፍራሽ፣ የዕቃ ማመላለሻ ጋሪዎችና የመሳሰሉ ቁሳቁሶችን ጥር 21 እና 22/2014 ዓ.ም በወልድያ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት ድጋፍ አድርጓል፡፡ የቁሳቁስ ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን 2.5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለወልድያ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዙር የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
- Details
ተማሪ ጽጌሬዳ ግርማይ ከአባቷ ከአቶ ግርማይ ገ/መድኅን እና ከእናቷ ከወ/ሮ ያበሻ ያዘዘው ወልቃይት ወረዳ አዲ ረመጽ ከተማ በ1993 ዓ/ም ተወለደች፡፡
ተማሪ ፅጌሬዳ ግርማይ የመሰናዶ ትምህርቷን በወልቃይት ጌታቸው አዘናው 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትላለች፡፡ ፎቶዎችን ለማየት
- Details
በዩኒቨርሲቲ ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ከ13 የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ለተወጣጡ መምህራን ‹‹Solid work››፣ ‹‹Arc cad›› እና ‹‹Auto cad›› በተሰኙ የኮንስትራክሽን ሶፍትዌሮች ዙሪያ ከጥር 16-20/2014 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡