ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ፣ በ2ኛና በ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ያሠለጠናቸውን 6,730 ተማሪዎች ለ34ኛ ጊዜ መስከረም 29/2014 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የፕሮፌሰርነት አካዳሚክ ማዕረግ ለአንድ መምህርና ተመራማሪም ሰጥቷል። ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ   

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መስከረም 24/2014 ዓ/ም በተካሄደው 6ኛው ሀገራዊ የመንግሥት ምሥረታ ክቡር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመመረጥዎ የተሰማውን ደስታ እየገለጸ የኃላፊነትዎ ዘመን የኢትዮጵያ ብልፅግና የሚረጋገጥበት፣ የከፍታና የስኬት እንዲሆን በመላው የዩኒቨርሲቲው መኅበረሰብ ስም የመልካም ምኞት መልዕክቱን ያስተላልፋል። 

የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ከቱሪዝምና ሆቴል ማኔጅመንት ት/ክፍል ጋር በመተባበር በቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ማኔጅመንት የ2ኛ ዲግሪ ትምህርት ለመክፈት የሚያስችል የውጭ ሥርዓተ-ትምህርት ግምገማ መስከረም 20/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ   

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሠለጠናቸውን 5 ሺህ ያህል ተማሪዎች በ3ኛ፣ በ2ኛ እና በመጀመሪያ ዲግሪ መርሃ-ግብሮች መስከረም 29/2014 ዓ.ም በዓባያ ካምፓስ ስቴዲዬም ለ34ኛ ዙር እንዲሁም የሳውላ ካምፓስ ተማሪዎችን መስከረም 30/2014 ዓ.ም በሳውላ ካምፓስ ለ4ኛ ዙር በደማቅ ሁኔታ ያስመርቃል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የ4ኛ ዓመት የኤሌክትሪካልና ኮምፕዩተር ምኅንድስና ተማሪዎች ከ2014 ዓ/ም ተመራቂ ባቾች ጋር እኩል እንዲመረቁ ለማድረግ ከሌሎቹ ተማሪዎች ቀድመው ወደ ኢንስቲትዩቱ በመግባት የ2ኛ ሴሚስተር ትምህርታቸውን በመጨረስ ለኢንተርንሺፕ እንዲወጡ ይቻል ዘንድ የፋከልቲው ተማሪዎች ቅድመ ዝግጅት በማድረግ መስከረም 30/2014 ዓ/ም ወደ ካምፓስ እንድትገቡና ከሰኞ ጥቅምት 01/2014 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት የሚጀመር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

    የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት