የዩኒቨርሲቲው ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከሆላንድ ማስትሪች ዩኒቨርሲቲ ጋር የ3ኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞችን በጋራ ለመክፈት ጳጉሜ 2/2013 ዓ/ም ስምምነት ተፈራርሟል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ  

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በአርባ ምንጭ ከተማ መንገድ ዳር ካሉና ለትራፊክ አደጋ ተጋላጭ ከሆኑ 10 ትምህርት ቤቶች ለተወጣጡ 60 የተማሪ ትራፊክ ፖሊሶች ጳጉሜ 3/2013 ዓ/ም የደንብ ልብስ ድጋፍ አድርጓል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ አገልገሎት ዳይሬክቶሬት ከሁሉ አቀፍ ሴክተር ዳይሬክቶሬትና ከአርባ ምንጭ ከተማ ወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በአደንዛዥ ዕፅና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከከተማው 12 ቀጠናዎች 6 ቀበሌያት ለተወጣጡ ወጣቶች ከነሐሴ 19-20/2013 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ  

የቆላማ አካባቢ በሽታዎች ሀገር አቀፍ ዓመታዊ የምክክር ጉባዔ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከነሐሴ 18-21/2013 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ በጉባዔው በወላይታ ዞን በሙከራ ላይ የሚገኘው የʻʻGeshiyaroʼʼ ፕሮጀክት አሁናዊ የመስክ ምልከታና የፕሮግራሙ የ2013 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ     

ዶ/ር ዮሴፍ ብሩ ገ/ጊዮርጊስ በቀድሞው ጅማ ክ/ሀገር ጅማ ከተማ ሐምሌ 29/1961 ዓ.ም ተወለዱ፡፡ የ1ኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በጅማ ከተማ ተከታትለዋል፡፡