የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 በጀት ዓመት ዓመታዊ ዕቅድ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት በተገኙበት ሐምሌ 15/2013 ዓ/ም ተገምግሞ ጸድቋል፡፡ ከካውንስል አባላቱ በዕቅዱ ላይ ሊሻሻሉ፣ሊካተቱና ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ነጥቦች ቀርበዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በ2013 ዓ.ም በዋናው ግቢ በቴክኖሎጂና ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ለተመደቡ 1,100 አዲስ ገቢ ተማሪዎች በቤተ-መጻሕፍት፣ በሬጅስትራርና በተማሪዎች አገልግሎት ዘርፍ አጠቃቀም እንዲሁም በተማሪዎች የዲሲፕሊን መመሪያ ዙሪያ ሐምሌ 16/2013 ዓ.ም ኦረንቴሽን ተሰጥቷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ