የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኅብረት በአባያ ክ/ከተማ በኩልፎ ቀበሌ ለተገኙ በርካታ አረጋዊያንና ወላጅ አጥ ሕፃናት የ2007 .ም የፋሲካ በዓልን በማስመልከት የምሳ ግብዣ አድርጓል፡፡

የሰጪ እጅ ሁሌም ከላይ ነው” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን የምሳ ግብዣ ያሰናዱት የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝደንት ተማሪ ጌትነት ዓለሙና የተማሪዎች ዲስፕሊን ተጠሪ ተማሪ ታመነ ዳኘው ናቸው፡፡ ተማሪ ጌትነት ባደረገው ንግግር የአ//ዩን ተማሪዎች ወክሎ ከታዳሚዎቹ መሃል በመገኘት በዓሉን ማክበሩ እንዳስደሰተውና ለወደፊትም በተመሳሳይ መልክና የበለጠ አቅም በመፍጠር በዓላትን በጋራ ለማሳለፍ እንደሚሠሩ ተናግሯል፡፡

በአባያ ክ ከተማ የኩልፎ ቀበሌ ወጣቶችና ስፖርት ዘርፍ ኃላፊ ወጣት ተክሌ ብርሃነገነት እና የአርባ ምንጭ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ ቤት ምኃላፊና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ወጣት በላይ ግዛቸው የአዩ ተማሪዎች ኅብረት ያደረገውን ድጋፍ አመስግነው ለወደፊትም መሰል ትብብርና በጋራ የመሥራቱ ልምድ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ በዝግጅቱ መጨረሻም የአ ዩ ተማሪዎች ኅብረት ለተሳታፊ ስፖንሰሮች የተሰጠውን የምሥክር ወረቀት ወስዷል፡፡

 

በተመሳሳይም የአ//ዩ ከፍተኛ የአስተዳደር አካላት በ5ቱም ካምፓሶች ከተማሪዎች ጋር በመሆን የፋሲካን በዓል በድምቀት አክብረዋል፡፡ በዋናው ግቢ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ ከሌሎች የአስተዳደር አካላት፣ የተማሪዎች ፕሬዝደንትና የተማሪዎች ተወካይ ኮሚቴዎች ጋር በመገኘት በዓሉ ደማቅ እንዲሆንና ተማሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዳሉ እንዲሰማቸው የሚያደርግ ድባብ ፈጥረዋል፡፡

በሌሎቹም ካምፓሶች የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮሌጅ ዲኖችና የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እንዲሁም የተማሪዎች ተወካዮች ከተማሪዎች ጋር በመሆን በዓሉ በልዩ ድምቀት እንዲከበር አድርገዋል፡፡