ወ/ሪት ብርቱካን ቡሣ ከአባታቸው ከአቶ ቡሣ ግዛው እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ብዙአየሁ እሸቴ በኮንሶ ወረዳ ጥር 6/1972 ዓ/ም ወለዱ፡፡ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በሀይሌ ደጋጋ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት ተከታትለዋል፡፡
ወ/ሪት ብርቱካን ቡሣ በሰው ሀብት አመራር የት/ት መስክ ከቅድስተ ማሪያም ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በ2003 ዓ/ም በ10+3 በዲፕሎማ የተመረቁ ሲሆን ግንቦት 5/1999 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ቤተ-መጽሐፍትና ዶክሜንቴሽን በሠርኩሌሽን አቴንዳንትነት በኮንትራት ተቀጥረዋል፡፡
ከሰኔ 1/2005 ዓ/ም ጀምሮ በዚሁ ክፍል የመጽሐፍት ግምጃ ቤት ሠራተኛ ሆነው በማገልገል ላይ ሳሉ በደረሰባቸው ድንገተኛ የመኪና አደጋ ህዳር 12/2009 ዓ/ም በተወለዱ በ36 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲያችን በወ/ሪት ብርቱካን ቡሣ ድንገተኛ ሞት የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል !!
ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት