Print

ሀገራችን ኢትዮጵያ በመንግሥትና በሕዝብ ሁለንተናዊ ተሳትፎ እየገነባች የሚገኘው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 2ኛው ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት በመጠናቀቁ መላው የዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብና ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን!!

ግድቡ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለሀገራችን ዕድገት መፋጠን በሙሉ አቅም አገልግሎት መስጠት እስኪጀምር ለግንባታው የነበረው ሁለንተናዊ ሕዝባዊ ተሳትፎ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል። አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና ማኅበረሰቡም እንደ ከዚህ ቀደም ሁሉ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ቀሪ የግንባታ ሥራዎች እስከሚጠናቀቁ ድረስ አስፈላጊውን ሁሉ አስተዋፅዖ ማድረጋቸውን አጠናክረው የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጣለሁ።

ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት