አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሪፖርት የሚደረግበት ቀን ኅዳር 12/2014 ዓ.ም

ምዝገባ የሚካሄድበት ቀን ኅዳር 13 እና 14/2014 ዓ.ም

መደበኛ ትምህርት የሚጀመርበት ኅዳር 15/2014 ዓ.ም በመሆኑ፡-

· አስፈላጊውን የትምህርት ማስረጃ

· አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ የትራስ ልብስና የስፖርት ትጥቅ

· ስምንት 3 x 4 የሆነ ጉርድ ፎቶ እና

· ኮቪድ-19ን ለመከላከል የሚያስችል የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል (ማስክ) ይዛችሁ

እንድትመጡ እያሳወቅን ከተጠቀሰው ቀናት ውጭ ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እንገልጻለን፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት