Print

በ2014 የትምህርት ዘመን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ግንቦት 1 እና 2 ሲሆን ምዝገባ የሚካሄደው ግንቦት 3 እና 4 እንዲሁም ትምህርት የሚጀመረው ግንቦት 5 ቀን 2014 ዓ.ም ይሆናል፡፡

በመሆኑም ወደ ዩኒቨርሲቲው በምትመጡበት ጊዜ፡- 

በመያዝ ሳውላ ካምፓስ የተመደባችሁ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በሚገኘው ሳውላ ካምፓስ ሬጅስትራር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት፣ በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኙ ካምፓሶች የተመደባችሁ በየካምፓሶቻችሁ በሚገኙ የሬጅስትራር ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች በአካል ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ እያሳሰብን የተመደባችሁበት ካምፓስ መረጃ ከዩኒቨርሰቲው ድህረ-ገጽ www.amu.edu.et ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንዲሁም ከተጠቀሱት ቀናት ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡

      የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት