ዶ/ር ብሩክ አማረ ስራቴ ከአባታቸው ከአቶ አማረ ስራቴ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አልማዝ አበበ በጋሞ አውራጃ አርባ ምንጭ ከተማ መስከረም 6/1977 ዓ/ም ተወለዱ፡፡ 

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምኅንድስና እና ሂሳብ (STEM) ማዕከል ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከማኅበረሰብ ጉድኝት ዋና ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ከጋሞ፣ ጎፋ፣ ቡርጂ፣ አማሮ፣ ኮንሶ፣ ባስኬቶ፣ደራሼና አሌ ዞኖች ለተወጣጡና ከ7ኛ- 12ኛ  ክፍል ለሚገኙ ተማሪዎች ከነሐሴ 1-30/2015 ዓ/ም ሲሰጥ የቆየው የተግባር ተኮር ሥልጠና ጳጉሜ 1/2015 ዓ/ም ተጠናቋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድኅረ ምረቃ ትምህርት ቤት በ2016 የትምህርት ዘመን በመደበኛ፣ በማታ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ-ግብሮች መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን ከሐምሌ 24 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 27 ቀን 2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራርና አሉምናይ ዳይሬክቶሬት በኩል በአካል እንዲሁም በመረጃ መረብ https://forms.gle/vG9KfojLfCXkgZYU9 በኩል ምዝገባ መፈጸሙ ይታወቃል፡፡


በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በባዮሎጂ ት/ክፍል በ ̋Biotechnology” ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ሳምሶን ትዕዛዙ የ3 ዲግሪ ትምህርቱን ማጠናቀቂያ የምርምር ሥራውን መስከረም 4/2016 ዓ/ም የውጭና የውስጥ ገምጋሚዎች በተገኙበት አቅርቧል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ እንኳን ለ2016 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡ አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤና እና የስኬት ይሁንላችሁ፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡