ከመስከረም 05-12/2008 ዓ/ም ለአንድ ሣምንት የሚቆየው የከፍተኛ ትምህርት ማህበረሰብ ሥልጠና በዩኒቨርሲቲው ሦስት የተለያዩ አዳራሾች እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ስልጠናው አምስት የተለያዩ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት የሚመክር ሲሆን ለውይይት አመቺ እንዲሆን ሠልጣኞች በበርካታ ቡድኖች ተከፋፍለዋል፡፡ የሥልጠናዉን ተሳታፊዎች በከፍል ለማየት እዚህ ይጫኑ

ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና የአስተዳደር ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች በመሉ፡- በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄደው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማህበረሰብ ስልጠና ለዩኒቨርሲቲያችን መምህራንና የአስተዳደር ድጋፍ  ሰጪ ሠራተኞች ከመስከረም 05-12/2009 ዓ/ም በተለያዩ ካምፓሶች በተዘጋጁ ጊዜያዊ መድረኮች የሚሰጥ በመሆኑ ሁሉም ተሳታፊ በየምድብ የስልጠና መድረክ ያለመንጠባጠብ በጊዜ በመገኘት የስልጠናው ተካፋይ እንዲሆን በአጽንዖት ያሳስባል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ

ዩኒቨርሲቲው ከደ/ብ/ብ/ህ/ክ/መ/ አርብቶ አደር ጉዳዮች ቢሮ ጋር በመተባበር በአነስተኛ መስኖ አስተዳደርና አጠቃቀም ለ6 ወራት ያሠለጠናቸውን 30 ሠልጣኞች ግንቦት 13/2008ዓ.ም አስመርቋል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከዩናይትድና ከብራይት ኮንስትራክሽን ድርጅቶች ጋር የ2ኛ ዙር የሳውላ ካምፓስ የግንባታ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ውል ሰኔ 28/2008 ዓ.ም ተፈራርሟል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ከህግ ት/ቤት ጋር በመተባበር በደቡብ ኦሞ ዞን ለሚገኙ የማረሚያ ቤት ኃላፊዎችና ሠራተኞች በመሰረታዊ የታራሚዎች መብትና አያያዝ ሰኔ 10/2008 ዓ.ም የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡