ዩኒቨርሲቲው ከጋሞ ዞን ሰላምና ፀጥታ ግንባታ መምሪያ ጋር በመተባበር ‹‹ሁሉ አቀፍ የማኅበረሰብ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም›› በሚል መሪ ቃል በቁጫ ወረዳ ሰላም በር ከተማ የካቲት 24/2013 ዓ.ም የመጀመሪያ ዙር ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

ሥልጠናው ‹‹ሁሉ አቀፍ ማኅበረሰብ ለዘላቂ ሰላም ግንባታ›› እና ‹‹በሃይማኖቶች መካከል መቻቻልና መከባበር›› በሚሉ ይዘቶች ዙሪያ መሰጠቱን የጋሞ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ የግጭት ዘላቂ መፍትሄ ሥራ ትግበራ ከፍተኛ ባለሙያና አሠልጣኝ አቶ መሰለ እንግዳ ተናግረዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በእጅ የሚሠራ ቀላል የኦቾሎኒ መፈልፈያ ማሽን አዘጋጅቶ በጋሞ ዞን ቁጫ ወረዳ ኦቾሎኒ አምራች ለሆኑ አርሶ አደሮች ለሙከራ በማቅረብ አጠቃቀሙን አስመልክቶ የካቲት 24/2013 ዓ.ም በሰላምበር ከተማ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡   ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ከየካቲት 30 - መጋቢት 2/2013 ዓ/ም ሥልጠናዊ ውይይት አካሂዷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በማድረግ ስለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከምሥረታው ጀምሮ አሁን እስካለበት የምርምር ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ድረስ ያለውን አጠቃላይ ሂደት ገለጻ አድርገዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 8ኛውን ዓመታዊ የጥናትና ምርምር ግምገማ ከየካቲት 26-27/2013 ዓ/ም አካሂዷል፡፡

የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ተ/ፕ በኃይሉ መርደኪዮስ በእንኳን ደኅና መጣችሁ ንግግራቸው የጥናትና ምርምር ሥራ የማኅበረሰቡን ችግር ለመፍታትና የመፍትሄ አቅጣጫ ለመጠቆም እንደሚረዳ ገልጸዋል፡፡ የምርምር ሥራዎች መበራከት የሚበረታታ በመሆኑ ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሚጠቅሙ ምርምሮችን መሥራት የመጀመሪያ ምርጫ መሆን አለበት ብለዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Arba Minch University has hosted Ministry of Science and Higher Education’s (MoSHE) 2-day training for 45 Ethiopian Government universities’ presidents, vice presidents and scientific directors from 9th to 10th March, 2021, at Main Campus. Deliberation on Ethiopia’s 10-year Strategic Planning on education roadmap, its implementation, evaluation and challenges involved were on the agenda. Click here to see the photos