በሥሩ 6 ፕሮጀክቶችን ይዞ ላለፉት 5 ዓመታት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና አካባቢው ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን ሲሠራ የቆየው IUC ፕሮግራም በገለልተኛ አካላት በተደረገ የአፈፃፀም ግምገማ የላቀ ውጤት በማስመዝገቡ የ2ኛ ዙር የ5 ዓመት ዕድል ማግኘቱ ተገልጿል፡፡

የፕሮግራሙ ኃላፊ ዶ/ር ፋሲል እሸቱ እንደገለጹት IUC ፕሮግራም በሁለት ዙር የተከፈለ የ10 ዓመት ቆይታ ያለው ሲሆን 2ኛው ዙር ዕድል የሚወሰነው በመጀመሪያው ዙር በሚመዘገበው ውጤት ነው፡፡ በዚህም መሠረት ላለፉት ዓመታት የተማሪዎችን ውጤታማነት፣ የፋይናንስና የአፈፃፀም ሪፖርቶችንና ሌሎችም ሥራዎችን በለጋሽ አካሉ ተመርጦ የመጣው ገለልተኛ ገምጋሚ ቡድን በአካል በመገኘት ባደረገው የአፈፃፀም ግምገማ ፕሮግራሙ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ በመቻሉ 2ኛ ዙር ዕድል ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው የምርምር ዳይሬክቶሬት ከቴክኖሎጂና ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ለተወጣጡ መምህራንና ተመራማሪዎች በምርምር አጻጻፍ ሳይንሳዊ ስነ-ዘዴ ዙሪያ ከየካቲት 9-11/2013 ዓ.ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ የምርምር ንድፈ ሃሳብ አሰባሰብና አጻጻፍ፣ የምርምር ግኝቶች አዘገጃጀትና አጻጻፍ እንዲሁም በታወቁ ጆርናሎች ላይ የሚወጡ ምርምሮች አጻጻፍ ስነ-ዘዴ የሥልጠናው ትኩረቶች ናቸው፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ነፃ፣ ገለልተኛና ብቃት ያለው የአገልግሎት ዘርፍን በተቋማት ውስጥ ለማጠናከር የሚረዳ የአሠልጣኞች ሥልጠና በሰው ሀብት ልማትና አስተዳደር እና በተቋማዊ ለውጥ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ጥር 27/2013 ዓ.ም ለዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት ተሰጥቷል፡፡

ነፃ፣ ገለልተኛና ብቃት ያለው የአገልግሎት ዘርፍ ግንባታ፣ የሰው ሀብት ልማትና ብቃት ማረጋገጫ ሥርዓት፣ የመንግሥት አገልግሎት እሴት ግንባታ እንዲሁም ሥነ-ምግባርና ጥራት ያለው የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ሥልጠናው በዋናነት ትኩረት ያደረገባቸው ነጥቦች ናቸው፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ለ2012 ዓ/ም 1ኛ ዓመት ለነበራችሁ ተማሪዎች በሙሉ

የሁሉም ካምፓሶች የ2012 ዓ/ም የ1ኛ ዓመት ተማሪዎች ሪፖርት የማድረጊያ ጊዜ ከየካቲት 16-18/2013 ዓ/ም ቀደም ብሎ በማስታወቂያ የተገለጸ ሲሆን ትምህርት የካቲት 22/2013 ዓ/ም የሚጀመር መሆኑን እያሳወቅን ሁሉም የ2012 ዓ/ም የ1ኛ ዓመት የነበራችሁ ተማሪዎች ከሁሉም ካምፓሶች በሕክምናና ፋርማሲ ትምህርት ዘርፍ የተመደባችሁ ሪፖርት የምትታደርጉት በነጭ ሳር ካምፓስ፣ በእንጂነሪንግ የተመደባችሁ በዋናው ካምፓስ፣ ቀደም ሲል በዋናው ካምፓስ ሆናችሁ በእንጂነሪንግ ያልተመደባችሁ በሙሉ በዓባያ ካምፓስ፣ ከሳውላና ጫሞ ካምፓሶች በሕግ የተመደባችሁ በጫሞ ካምፓስ ሆኖ ሌሎቻችሁ በነበራችሁበት ካምፓስ ሪፓርት የምታደርጉ መሆኑን እንገልጻለን።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት

Having prospected Bonke and Gerese woredas, College of Natural Sciences’ Department of Geology has again explored Konso woreda’s Kolme cluster situated in Segan Area People’s Zone for South Nations Nationalities and People’s Region Mines and Energy Bureau wherein its team found that study area’s high-grade metamorphic rocks hold minerals such as quartz, feldspar, mica and also low concentration of gold, informed University-Industry Linkage & Technology Transfer Directorate’s Director, Dr Tolera Seda. Click here to see the photos