Arba Minch University’s 33rd Convocation to be hosted virtually for its Master graduating class for 2020 at New Hall, Main Campus wherein a few will be officiating the ceremony led by university President, Dr Damtew Darza, Gamo Zone Administrator, Mr Birhanu Zewude, Jinka University President, Prof Gebre Entiso, Arba Minch Town Mayor, other invited guests & officials; while graduates, their near and dears and others can view it via online portals such as Facebook and YouTube from 8.30 onwards at their homes.

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት 39ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ከነሐሴ 21-23/2012 ዓ/ም ድረስ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለ3 ቀናት ተካሂዷል፡፡

መርሃ-ግብሩን በአገር ባህልና ወግ መሠረት መርቀው የከፈቱት የጋሞ አባቶች ባስተላለፉት መልዕክት ዩኒቨርሲቲዎች ሀገርንና ዓለምን የሚለውጡ አዳዲስ ሐሳቦችና ፈጠራዎች የሚፈልቁበት ቦታ እንጂ ተማሪዎች በቋንቋ፣ በብሄርና በሐይማኖት እየተከፋፈሉ የሚጣሉበት ሥፍራ እንዳይሆንና በተቋማቱ ከዚህ ቀደም እየታዩ የነበሩ የሠላም መደፍረሶች እንዳይከሰቱ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ የተማሪዎች ኅብረትና ሌሎችም የሚመለከታቸው ሁሉ አካላት ለሠላም ዘብ በመቆም የአገራችን ብልፅግና እንዲረጋገጥ በትኩረት እንዲሠሩ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከትምህርት ሚኒስቴር ለተገኙ ተወካዮች በባህሉ መሠረት ጥብቅ አደራ ከእርጥብ ሣር ጋር በመስጠት ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ የብሄር ማንነታችን የሚያብበው እንደ ሀገር ኢትዮጵያ ስትኖር ነው ያሉት አባቶቹ ሁላችንም ኢትዮጵያ በምትባል ምድር ላይ የተዘራን የሰብል ዓይነቶች በመሆናችን የሀገራችንን ህልውና ልናስጠብቅ እንደሚገባ በአጽንዖት ተናግረዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የፊዚክስ ትምህርት ክፍል በማቴሪያል ፊዚክስ የዶክትሬት ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራም ለመክፈት የውጭ ሥርዓተ ትምህርት ነሐሴ 18/2012 ዓ/ም ግምገማ አካሂዷል፡፡

የአካዳሚክ ጉ/ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ ትውልድና የምርምር ዩኒቨርሲቲ እንደመሆኑ የ2ኛና 3ኛ ዲግሪ ፕሮግራሞችን በማስፋፋትና በጥራት መስጠት ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሠራ የቆየ ሲሆን በፊዚክስ ትምህርት መስክ የሚከፈተው የ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራምም የዚሁ ሥራ አካል ነው ብለዋል፡፡ አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች ሲከፈቱ የሥርዓተ-ትምህርቱ ዝግጅት በርካታ ሂደቶችን እንደሚያልፍ የገለፁት ዶ/ር የቻለ ፕሮግራሞችን መክፈት በራሱ ግብ ባለመሆኑ ሥርዓተ-ትምህርቱን በየጊዜው የመከለስ እንዲሁም ትምህርቱን በጥራት መስጠትና ምርምር ተኮር የማድረግ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ በመሆኑ በቀጣይነት ይሠራል ብለዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እያስገነባ የሚገኘውን የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታን በ2013 በጀት ዓመት በከፊል ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የሆስፒታሉን የግንባታ ሂደት ነሐሴ 15/2012 ዓ/ም በጎበኙበት ወቅት ተገልጿል፡፡

በ2007 ዓ/ም የተጀመረው የሆስፒታሉ ግንባታ በዲዛይን ማስተካከያና ተጨማሪ ግንባታ፣ በሆስፒታሉ ግንባታ ቦታ ተነሺዎች፣ የክፍያዎች መዘገየት፣ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ የዋጋ ንረት፣ በግንባታ አካባቢ የሚገኙ የመብራት፣ የውሃና የስልክ መስመሮች እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች ይጠናቀቃል ከተባለበት ጊዜ የዘገየ ሲሆን እስካሁን ባለው ሂደት 77 በመቶ የግንባታ ሂደት መጠናቀቁ በጉብኝቱ ወቅት ተጠቅሷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በዩኒቨርሲቲው የሚገኙ የገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዞችን ሐምሌ 20/2012 ዓ/ም ጉብኝተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስና ልማት ም/ፕሬዝደንት ወ/ሮ ታሪኳ ወ/መድኅን ጉብኝቱ በዩኒቨርሲቲው ያሉ የተለያዩ የገቢ ማመንጫ ተቋማት ያሉበትን የአፈፃፀም ደረጃና ችግሮች በአካል በማየት ለቀጣይ ሥራዎች አቅጣጫና ውሳኔ ለመስጠት የሚረዱ ሀሳቦች ለማግኘት የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የራሳቸውን ገቢ በማመንጨት ወጪያቸውን በከፊል እንዲሸፍኑ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በ2007 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው የእንጨትና ብረታ ብረት፣ የሕትመትና የግብርና ኢንተርፕራይዞች ተመስርተው ሲሰሩ መቆየታቸውን ያስታወሱት ም/ፕሬዝደንቷ መሰል ጉብኝቶች መደረጋቸው የዘርፉን ወጤታማነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ናቸው ብለዋል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ