የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥነ ትምህርትና ሥነ ባሕርይ ሳይንስ ትምህርት ቤት የምርምር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በትምህርት ቤቱ ከዚህ ቀደም ተጀምረው በተያዘላቸው ጊዜና በጀት መሠረት ባልተጠናቀቁ የምርምር ሥራዎች ላይ የካቲት 14/2016 ዓ/ም ዓመታዊ ግምገማ አካሂዷል፡፡  ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በ‹‹Computing and Software Engineering›› ፋከልቲ ለተመደቡ አዲስ የ2 ዓመት ተማሪዎች የእንኳን ደኅና መጣችሁ አቀባበልና የ‹‹Computing and Software Engineering Club/ CaSE Club/ ትውውቅ መርሃ ግብር የካቲት 13/2016 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

Arba Minch University Senate promoted five academic staff of College of Natural and Computational Sciences to Associate Professorship Academic Rank position on February 22/2024. Click here to see more photos.

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በዘንድሮው ዓመት የሚያስመርቃቸው የሕክምና ዶክተሮች ሀገር አቀፉን የመውጫ ፈተና መቶ በመቶ ማለፍ ችለዋል፡፡ የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር ዓለማየሁ ጩፋሞ በተገኘው ውጤት የተሰማቸውን ደስታ በዩኒቨርሲቲው ስም እየገለጹ ለተመራቂ የሕክምና ዶክተሮች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በውኃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የማኅበረሰብ ጉድኝት ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ሦስት ፕሮጀክቶች የደረሱበት ደረጃ የመጀመሪያ ዙር ግምገማ የካቲት 08/2016 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ