አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን በቅድመ ምረቃ 193 እና በ2ኛ ዲግሪ 6 በድምሩ 199 ተማሪዎችን ሰኔ 26/2014 ዓ.ም አስመርቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 89ኙ ሴቶች ናቸው፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና በ2ኛ ዲግሪ መርሃ ግብሮች በመደበኛ፣ በማታ፣ በክረምት፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይና ርቀት፣ እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 2,561 ተማሪዎችን ሰኔ 25/2014 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 662ቱ ሴቶች ናቸው፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት ሰኔ 23/2014 ዓ/ም ባደረገው ስብሰባ በመጀመሪያና በ2ኛ ዲግሪ መርሃ ግብር በመደበኛ፣ በማታ፣ በክረምት፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይና ርቀት እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 2,540 ተማሪዎችን ቅዳሜ ሰኔ 25/2014 ዓ/ም እና እሁድ ሰኔ 26/2014 ዓ/ም እንዲመረቁ ወስኗል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 3ኛውን ሀገራዊ ዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ፎረም ‹‹የቴክኖሎጂ ሽግግርና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ የዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስርን ማሳደግ›› በሚል መሪ ቃል ሰኔ 21/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡

ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት የትውውቅ እንዲሁም ለቀድሞ የቦርዱ አባላት የምስጋናና የሽኝት መርሃ ግብር ሰኔ 11/2014 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡