- Details
ዩኒቨርሲቲው ከአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የማንጎ ማውረጃ ቴክኖሎጂ ጥር 28/2016 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ኦቾሎ ላንቴ ቀበሌ ለሚገኙ አርሶ አደሮች ለሙከራ አቅርቧል፡፡ የቴክኖሎጂዎቹን አጠቃቀም አስመልክቶ በባለሙያዎች ገለጻ በማድረግ ሁለት የማውረጃ መሣሪያዎችን በቡድን የተከፈሉ አርሶ አደሮች የተረከቡ ሲሆን ከአርሶ አደሩ የሚመጣውን ግብረ መልስ ተከትሎ ማሻሻያ ታክሎ በስፋት ለማዳረስ እንደሚሠራ ተገልጿል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማንጎ ማውረጃ ቴክኖሎጂን ለአርሶ አደሩ ለሙከራ አቀረበ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በምርምር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት አዘጋጅነት ከተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ለተወጣጡ የኮሌጁ መምህራንና ተመራማሪዎች ከጥር 23 - 26 ለአራት ተከታታይ ቀናት የጂአይኤስ አጠቃቀም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ለሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራንና ተመራማሪዎች በጂአይኤስ/GIS/ ዙሪያ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣንና ከጋሞ ዞን ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር “የጋሞ ዱቡሻ እና የዱቡሻ ዎጋ˝ ሥርዓት የጥናትና ምርምር ማስጀመሪያ የማኅበረሰብ ንቅናቄ መድረክ ጥር 25/20/16 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: “የጋሞ ዱቡሻ እና የዱቡሻ ዎጋ" የጥናትና ምርምር ማስጀመሪያ የማኅበረሰብ ንቅናቄ መድረክ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት የአምሳለ ፍርድ ቤት ፍጻሜ ውድድር ጥር 23/2016 ዓ/ም ያካሄደ ሲሆን ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ውድድር ኢትዮጵያንና አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን በመወከል በታንዛንያ አሩሻ በተደረገው ጠቅላላ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ውድድር ተሳትፈው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ዕውቅና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ለጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የፎረንሲክ ሜዲስንና ቶክሲኮሎጂ ስፔሻሊቲ ተማሪዎች ከታኅሣሥ 18 - ጥር 24/2016 ዓ/ም በሁለት ዙሮች የፎረንሲክ ናሙና ምርመራ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ለፎረንሲክ ሜዲስንና ቶክሲኮሎጂ ስፔሻሊቲ ተማሪዎች የፎረንሲክ ናሙና ምርመራ ሥልጠና ተሰጠ