የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፐብሊክ ዲፐሎማሲ ማዕከል ‹‹የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አሠራር፣ የሚዲያ አተገባበርና ንቃት›› በሚል ርዕስ ከዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች ለተወጣጡ ከ200 በላይ ተማሪዎች ሰኔ 10/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ትምህርት ክፍሎች የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ እጩ ዶክተሮች ከሰኔ 4-8/2014 ዓ.ም የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎች በተገኙበት የመመረቂያ ጽሑፎቻቸውን አቅርበዋል፡፡ የምርምር ሥራቸውም አስፈላጊውን መስፈርት አሟልቶ በመገኘቱ በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነትን አግኝቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ-ምረቃ ትምህርት ቤት በ2014 የትምህርት ዘመን በክረምት መርሐ ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን ከዚህ በታች በተጠቀሱት የትምህርት መስኮች ተቀብሎ ማሰልጠን ይፈልጋል፡፡

‹‹በተፈጠረው እድል ማኅበረሰባችንን እናገልግል›› በሚል መሪ ቃል ዩኒቨርሲቲው 7ኛውን የማኅበረሰብ ሳምንት ከሰኔ 06-12/2014 ዓ/ም በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብሯል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ክርስቲያን ኤይድ/Christian Aid /ከተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በካምባ ወረዳ ዲንጋሞ ቀበሌ ማይጸሌ ወንዝ ላይ አነስተኛ የኃይል ማመንጫ ለማስገንባት ሰኔ 12/2014 ዓ/ም የመሠረት ድንጋይ አስቀምጧል፡፡ ለሥራው ማስፈፀሚያ የሚሆነው ገንዘብ 1.1 ሚሊየን ብር በዩኒቨርሲቲውና 6.123 ሚሊየን ብር በክርስቲያን ኤይድ ግብረ ሠናይ ድርጅት የሚሸፈን ይሆናል፡፡