በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ መምህራን የተገኘ የምርምር ውጤት ላይ ተመሥርቶ ኮሌጁ ከዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት፣ ከጃኖ ዕደ ጥበብ ኢንተርፕራይዝ እና ከGIZ ጋር በመተባበር በጨንቻ ዶኮ ማሾ ቀበሌ ለሚኖሩ ሸማኔዎች የዘመናዊ ሽመና አሠራር ላይ ከግንቦት 20 - ሰኔ 04/2014 ዓ/ም ለ15 ተከታታይ ቀናት የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በሥራ ላይ ልምምድ የቆዩ የኮሌጁ መምህራንን ሪፖርት ሰኔ 04/2014 ዓ/ም ገምግሟል፡፡ በዕለቱ ከመንግሥትና ከግል ድርጅቶች ጋር አብሮ ለመሥራት የሚያስችል የስምምነት መግባቢያ ሰነድም ተፈራርሟል፡፡

ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዲግሪ የክረምት መርሃ-ግብር ተማሪዎች በሙለ

የ2014 ዓ.ም የክረምት ትምህርት ምዝገባ ሐምሌ 4-5/2014 ዓ.ም ስለሚካሄድ በተጠቀሱት ቀናት
በየካምፓሶቻችሁ ተገኝታችሁ እንድትመዘገቡ እየገለጽን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን
ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ እንዲሁም ይህ ማስታወቂያ የግብርና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎችን
የማይመለከት መሆኑን ያስታውቃል፡፡


የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተከታታይና ርቀት ትምህርት ኮሌጅ

የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) እና የእንግሊዝ ተራድኦ ድርጅት (FCDO) ድጋፍ የሚያደርጉለት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ባዘጋጁት የዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትስስር የምርምር ውጤቶች ወደ ገበያ የሚገቡበት የገንዘብ ድጋፍ ውድድር ላይ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አሸናፊ ሆኗል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ