- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት በ2013 እና 2014 በጀት ዓመታት ወደ መኅበረሰብ ወርደው ትግበራ ላይ የሚገኙ የምርምር ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ግምገማ ግንቦት 30/2014 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በ2013 እና 2014 በጀት ዓመታት ምርምርን መነሻ በማድረግ ወደ ትግበራ የገቡ የምርምር ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሰገንና ጨልኮ ወንዞች ላይ የመስኖ ውሃ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክቶች ዲዛይንና ጥናት ለማካሄድ ከደቡብ ዲዛይን፣ ግንባታና ቁጥጥር ባለሥልጣን ጋር ግንቦት 26/2014 ዓ/ም ባለ ድርሻ አካላት በተገኙበት የውል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ የሰገን ወንዝ በኮንሶ ዞንና በቡርጂ ልዩ ወረዳ መካከል ሲሆን የጨልኮ ወንዝ ደግሞ በመሎ ኮዛ ወረዳ በቦረዳ ጋዘር የሚገኙ ናቸው፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የመስኖ ውሃ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክቶች ዲዛይንና ጥናት የውል ስምምነት ተፈራረመ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በሎጅስቲክ እና ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት ት/ክፍል መምህርና ተመራማሪ አቶ ሀቢብ ሳኖ “International Virtual Conference on Intelligent Computing in Humanity, Agriculture, Science & Technology” በሚል ርዕስ በተካሄደ ቨርቹዋል ኮንፈረንስ ላይ ቁልፍ ንግግር አቅርበዋል፡፡
Read more: በዓለም አቀፍ ቨርቹዋል ኮንፍረንስ ላይ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ ቁልፍ ንግግር ቀረበ
- Details
ማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ በ“ELT”፣ በ“Environment and Natural Resources Management” እና በ“Disaster Risk Management” ትምህርት ፕሮግራሞች በ3ኛ ዲግሪ ያሠለጠናቸውን ተማሪዎች ነገ ቅዳሜ ሰኔ/4/2014 ዓ/ም፣ የፊታችን ሰኞና ማክሰኞ ማለትም ሰኔ 6 እና 7/2014 ዓ/ም የመጨረሻ የምርምር ሥራቸውን የውጪና የሀገር ውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት የሚያቀርቡ ይሆናል፡፡
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ-ምረቃ ት/ቤት አስተባባሪነት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን አጠናቀው ለተመረቁ መምህራን 3ኛው የእንኳን ደኅና መጣችሁ ‹‹የዶክተሮች ቀን/Doctoral Day›› መርሃ-ግብር ግንቦት 30/2014 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ