አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹Christian Aid››/ክርስቲያን ኤይድ/ ከተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር የእንሰት አመራረትና ማብላላት ሂደትን ለማዘመን የሚረዱ በዩኒቨርሲቲው የተፈጠሩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ለማዳረስ 3.2 ሚሊየን ብር የተመደበለት ፕሮጀክት በትብብር እየሠሩ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የፕሮጀክቱን የሥራ እንቅስቃሴና አፈፃፀም አስመልክቶ ከድርጅቱ የመጣ ቡድን ግንቦት 16/2014 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ምልከታ አድርጓል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ለጫሞ ካምፓስ አዲስ ገቢ ሴት ተማሪዎች አቀባበልና የላቀ ውጤት ላመጡ የ3ኛ ዓመት ሴት ተማሪዎች የሽልማት መርሃ ግብር ግንቦት 11/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ 

ከታኅሣሥ 08/2014 ዓ/ም ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኅብረት ፓርላማ ምርጫ ግንቦት 14/2014 ዓ/ም አፈ-ጉባኤና ም/አፈ-ጉባኤ በመምረጥ ተጠናቋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሙያ መመሪያ እና የምክር ማዕከል (Career Guidance and Counseling Center) ደረጃ ዶት ኮም ኃ.የተ.የግ. ድርጅት /Dereja.Com/ እና አይ - ጆብ ሪክሪዩትመንት (I-Job Recruitment) ከሚባል የግል ድርጅት ጋር በመተባበር ለ2014 ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎች ከግንቦት 05-13/2014 ዓ/ም የሥራ ዝግጁነት /Job Readiness/ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የባህልና ቋንቋ ጥናት ተቋም ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ‹‹ስነ-ቃል ለሀገራዊ መግባባት›› በሚል ርዕስ ግንቦት 13/2014 ዓ/ም ሀገራዊ ሲምፖዚየም አካሂዷል፡፡