- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-ትምህርትና ሥነ-ባህሪ ሳይንስ ት/ቤት ለጊዶሌ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችና መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች የምልክት ቋንቋ ምንነት፣ የአካቶ ትምህርት ጽንሰ ሃሳብና አተገባበር፣ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች የማስተማሪያ ሥነ-ዘዴና ልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች የሚያስፈልጋቸው ጭብጦች ዙሪያ ከመጋቢት 14-15/2014 ዓ/ም በልዩ ፍላጎትና አካቶ ት/ክፍል መምህራን ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ፊዚክስ ት/ክፍል ከጋሞ ዞን ወረዳዎች ለተወጣጡ 29 የፊዚክስ መምህራን በኅዋ ሳይንስ ምርምር ዙሪያ እንዲሁም ለት/ክፍሉ የድኅረ ምረቃ ተማሪዎች የምርምር ጽሑፍ አዘገጃጀትን አስመልክቶ ከመጋቢት 14-17/2014 ዓ/ም የቆየ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
Read more: ከጋሞ ዞን ወረዳዎች የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተወጣጡ የፊዚክስ መምህራን በኅዋ ሳይንስ ዙሪያ ሥልጠና ተሰጠ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከግብርና ሳይንስ፣ ከተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ እና ከሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጆች ጋር በመተባበር 8ኛውን ሳይንስ ለዘላቂ ልማት ዓውደ ጥናት ከመጋቢት 30 - ሚያዝያ 01/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ በዓውደ ጥናቱ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተወጣጡ በግብርና፣ ጤና እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፎች የተዘጋጁ 58 ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ሴቶች በሚደርስባቸው ጾታዊ ትንኮሳ፣ አድልኦ፣ የሥራ ጫና፣ ከወንዶች እኩል አለመታየትና በሌሎችም ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ መጋቢት 21/2014 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡