አርበ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ጋር በመተባበር ‹‹አርባ ምንጭ ታንብብ›› በሚል መሪ ቃል ከጥር 18-21/2016 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ከተማ የንባብ ሳምንት አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የዩኒቨርሲቲው የሥራ ፈጠራ ልማት እና ማበልጸጊያ ማዕከል ከኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት/ Entrepreneurship Development Institute (EDI) ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጋር በመተባበር ከጥር 13-18/2016 ዓ/ም ለዩኒቨርሲቲው ሴት መምህራን የኢንተርፕርነርሽፕ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ሥልጠናው በኢንተርፕርነርሽፕ ምንነት፣ የቢዝነስ ፕላን አዘገጃጀት፣ የስኬታማ ኢንተርፕርነሮች ባህርያት እና መሰል ርእሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2016 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ዕቅድ ክንውን ሪፖርት ጥር 17/2016 ዓ/ም ለዩኒቨርሲቲው ካውንስል ቀርቦ ተገምግሟል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ ከ10 ዩኒቨርሲቲዎች ለተወጣጡ የሥነ ልቦና ባለሙያዎች እና የአካዳሚክ ፕሮግራም ዳይሬክተሮችና አስተባባሪዎች በተማሪ ልማት ዙሪያ ከጥር 16-17/2016 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡