የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ/ም የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ጥር 27/2014 ዓ/ም የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በአርባ ምንጭ ከተማ ከሚገኙ ት/ቤቶች ለተወጣጡ 100 የ7ኛና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ዓባያ ካምፓስና ዋናው ግቢ በሚገኙ ቤተ-ሙከራዎች በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምኅንድስናና ሒሳብ ትምህርት መስኮች ከጥር 28/2014 ዓ/ም ጀምሮ ለ15 ቀናት የሚቆይ የተግባር ሥልጠና እየሰጠ ነው፡፡  

በደ/ብ/ብ/ሕ/ክ መንግሥት ፍትሕ ቢሮና በክልሉ በሚገኙ 7 ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በጋራ በተከናወኑ የፍትሕና የሕግ አገልግሎት ሥራዎች አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የላቀ አፈጻጸም በማስመዝገብ የእውቅናና የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶለታል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እንግሊዝኛ ቋንቋና ስነ-ጽሑፍ ት/ክፍል ላላፉት 5 ዓመታት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩት እጩ ዶ/ር ማንጉዳይ መርጮ የካቲት 5/2014 ዓ/ም የውስጥና የውጪ ገምጋሚዎች በተገኙበት የምርምር ሥራቸውን አቅርበዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲው ሁሉ አቀፍ ሴክተር ዳይሬክቶሬት ከሰው ሀብት ልማትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ከ6ቱ ካምፓሶች የተለያዩ ሥራ ክፍሎች ለተወጣጡ አስተባባሪዎች፣ ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች ከየካቲት 01-02/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ በሥልጠናው የአእምሮ ዕውቀት፣ የስሜት ልህቀት፣ ስብእናና ተፈጥሯዊ ባህሪያት በስፋት ተዳሰዋል፡፡