አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሕወሓት ወራሪ ኃይል ከፍተኛ ጉዳት ላጋጠመው ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ማስተማር ሥራ የሚውሉ ላፕቶፖች፣ ወረቀቶች፣ ካኪ ፖስታዎች፣ እስክሪብቶዎች፣ ቾክ፣ የቢሮና የተማሪ ወንበሮች፣ የማስተማሪያ ጠረጴዛዎች፣ ለተማሪ የምግብ አገልግሎት የሚውሉ የካፍቴሪያ ዕቃዎች፣ የውሃ ማጠራቀሚያ ፕላስቲክ ጋኖች፣ የእንጀራ ምጣዶች፣ የፍራሽ፣ የዕቃ ማመላለሻ ጋሪዎችና የመሳሰሉ ቁሳቁሶችን ጥር 21 እና 22/2014 ዓ.ም በወልድያ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት ድጋፍ አድርጓል፡፡ የቁሳቁስ ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን 2.5 ሚሊየን ብር የሚያወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ተማሪ ጽጌሬዳ ግርማይ ከአባቷ ከአቶ ግርማይ ገ/መድኅን እና ከእናቷ ከወ/ሮ ያበሻ ያዘዘው ወልቃይት ወረዳ አዲ ረመጽ ከተማ በ1993 ዓ/ም ተወለደች፡፡

ተማሪ ፅጌሬዳ ግርማይ የመሰናዶ ትምህርቷን በወልቃይት ጌታቸው አዘናው 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትላለች፡፡  ፎቶዎችን ለማየት

በዩኒቨርሲቲ ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ከ13 የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ለተወጣጡ መምህራን ‹‹Solid work››፣ ‹‹Arc cad›› እና ‹‹Auto cad›› በተሰኙ የኮንስትራክሽን ሶፍትዌሮች ዙሪያ ከጥር 16-20/2014 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ 

በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴርና በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትብብር ‹‹ኑ የፈረሰውን የትውልድ ማፍሪያ ተቋም እንገንባ›› በሚል መሪ ቃል የዩኒቨርሲቲ ሕዝብ ግንኙነት ም/ፕሬዝደንት፣ ዳይሬክተሮችና የዘርፉ ባለሙያዎች ጥር 21/2014 ዓ/ም ውይይት አካሂደዋል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አውስትራሊያ ሀገር ከሚገኘው ‹‹Menzies School of Health Research›› ከተሰኘ የጤና ምርምር ት/ቤት ጋር ‹‹Effectiveness of Novel Approaches to Radical Cure of Vivax Malaria with Tafenoquine and Primaquine›› በሚል ርዕስ የሚያከናውኑትን ግራንድ የምርምር ፕሮጀክት መጀመር የሚያስችል በ‹‹Clinical Trial›› የምርምር ሥነ-ምግባርና ፕሮቶኮሎች ዙሪያ በምርምሩ ለሚሳተፉ ስፔሻሊስት ሐኪሞችና የጤና ባለሙያዎች ከት/ቤቱ በመጡ ባለሙያ ከጥር 13/2014 ዓ/ም ጀምሮ ለ5 ቀናት ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ