የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት በኃላፊነት ላይ ላሉ ሴት መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች የአመራርና የአስተዳደር ክሂሎት እንዲሁም ለጸሐፊዎችና የቢሮ ረዳቶች በሥርዓተ ጾታ፣ ጾታዊ ትንኮሳና ጥቃትን በመከላከል ላይ ከጥር 04 - 06/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ የጂኦግራፊያዊ መረጃ ሥርዓት፣ ሶፍትዌር፣ የዌብ ጂ.አይ.ኤስ (GIS)ና የጂኦዳታቤዝ አስተዳደር መተግበሪያዎች አቅራቢ ድርጅት ከሆነው ‹‹Environmental Systems Research Institute (ESRI)›› ጋር ባደረገው ስምምነት መሠረት ለመማር ማስተማር፣ ለምርምር፣ ለቴክኖሎጂ ፈጠራና አስተዳደራዊ ሥራዎች የሚውል ‹‹ArcGIS›› ሶፍትዌርን ለ3 ዓመታት በነፃ የመጠቀም ፈቃድ አግኝቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት ከግንባታ ዘርፍ ጋር የተያያዘ ትምህርት ለሚሰጡ መምህራን፣ የድኅረ ምረቃ ተማሪዎችና በዘርፉ እየሠሩ ላሉ የአርባ ምንጭ ከተማ ማዘጋጃ ቤትና የዩኒቨርሲቲው ባለሙያዎች ‹‹Effective Project Planning and Monitoring›› በሚል ርዕስ ከታኅሣሥ 25-26/2014 ዓ.ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛ ቋንቋና ስነ-ጽሑፍ ት/ክፍል መምህርና ተመራማሪ ዶ/ር መለሰ መንገሻ ‹‹EASY WAYS TO READ IN ENGLISH›› በሚል ርዕስ ከKG - 4ኛ ያለውን የክፍል ደረጃ መሠረት አድርጎ የተዘጋጀው የእንግሊዝኛ ቋንቋ ፍኖተ ንባብ አጋዥ መጽሐፍ ታኅሣሥ 26/2014 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ተመርቋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሕግ ሲታዩ የቆዩ የግድያ፣ የአስገድዶ መድፈር እና የአዳራሽ ወንበር ግዢ ክሶች የፍ/ቤት ውሳኔ የተሰጠባቸው መሆኑ ታኅሣሥ 13/2014 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው የሕግ አገልግሎት ዳይሬክተር ተገልጿል፡፡