የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ የ2013 ዓ/ም የሥራ አፈጻጸምን መሠረት በማድረግ በመማር ማስተማር፣ በጥናትና ምርምር፣ በማኅበረሰብ አገልግሎት እንዲሁም በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ከዩኒቨርሲቲው መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችና የካውንስል አባላት ጋር ከታኅሣሥ 7-9/2014 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት እና ከጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ ጋር በመተባበር በፎረንሲክ ወንጀል ምርመራ ዘዴና ማስረጃ አያያዝ ዙሪያ ከጋሞ ዞን ለተወጣጡ 36 የፎረንሲክ ምርመራ ፖሊስ መኮንኖች እንዲሁም ከዩኒቨርሲቲው ለተወጣጡ የጥበቃ ሠራተኞች ከታኅሣሥ 7-9/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የ2014 ዓ/ም የ1ኛ ተርም የአዲስ ተመዝጋቢዎች የ1ኛ ሴሚስተር የርቀት ትምህርት የምዝገባ፣ የቲቶሪያልና የፈተና መርሃ-ግብር ከዚህ ቀጥሎ ባለው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት በተመዘገባችሁበት ማዕከል የሚከናወን መሆኑን እየገለጽን በጊዜ ሠሌዳዉ መመዝገብ ያልቻለ ተማሪ በቅጣት መመዝገብ የሚችል መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የባዮ ቴክኖሎጂ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር አዲሱ ፈቃዱ በኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት በተደረገ ሀገር አቀፍ የምግብ ፈጠራ ሥራዎች ውድድር 1ኛ በመውጣት አሸናፊ ሆነዋል፡፡ ውድድሩ ከኅዳር 29 - ታኅሣሥ 1/2014 ዓ/ም ከተካሄደው ሀገር አቀፍ የሥነ-ምግብ ምርምር ኮንፍረንስ ጋር ተያይዞ የተደረገ ሲሆን በውድድሩ ከ11 ተቋማት የተወጣጡ የፈጠራ ሰዎች ተካፍለዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ-ጽሑፍ አማርኛ ት/ክፍል ጋር በመተባበር ለአርባ ምንጭ ከተማ ማረሚያ ተቋም፣ ለጨንቻ ከተማ ወጣቶች ቤተ-መጻሕፍትና በጨንቻ ለሚገኘው ሆሎኦና ላካ ሙሉ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ታኅሣሥ 6/2014 ዓ.ም የመጻሕፍት ድጋፍ አድርጓል፡፡ መጻሕፍቱ በቁጥር 433 ሲሆኑ የኢትዮጵያ ታሪክ፣ የተለያዩ ጀግኖች ታሪክ፣ ልብወለዶች፣ ማኅበራዊ ጉዳዮችን የሚዳስሱ፣ የቋንቋ እና የትምህርት ማጣቀሻዎችን የሚያካትቱ ናቸው፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ