የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል አውስትራሊያ ሀገር ከሚገኘው “Menzies School of Health Research” ከተሰኘ የጤና ምርምር ት/ቤት ጋር ‹‹Effectiveness of Novel Approaches to Radical Cure of Vivax Malaria with Tafenoquine and Primaquine›› በሚል ርዕስ 210 ሺህ ዶላር የተመደበለት ግራንድ የምርምር ፕሮጀክት ለማከናወን ጥቅምት 5/2014 ዓ/ም የመግባቢያ ስምምነት በቨርችዋል ተፈራርመዋል፡፡  

የዩኒቨርሲቲው ሁሉ አቀፍ ሴክተር ዳይሬክቶሬት ከአርባ ምንጭ ከተማ ለተወጣጡ በኤችአይቪ/ኤድስ ለተጎዱና አቅም ለሌላቸው 200 ተማሪዎች ጥቅምት 2/2014 ዓ/ም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ባህልና ቋንቋ ጥናት ተቋም 2ኛውን ዓለም አቀፍ የኦሞቲክ ቋንቋ ዓውደ ጥናት ከጥቅምት 01-02/2014 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ በዓውደ ጥናቱ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት በኦሞቲክ ቋንቋ ላይ የተሠሩ 17 ጥናቶች ቀርበው የቋንቋው ተናጋሪዎች ባሉበት ተገምግመዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ   

ከመስከረም 5 - ጥቅምት 5 የነበረው የ2ኛው ዙር ብሩህ የፈጠራ ሃሳብ ውድድር የማመልከቻ ጊዜ እስከ ጥቅምት 20/2014 ዓ/ም የተራዘመ ስለሆነ በውድድሩ ለመሳተፍ የጊዜ እጥረት ያጋጠማችሁ ተሳታፊዎች ለውድድሩ ተብሎ በተዘጋጀው ድረ-ገጽ www.bruh.et.com ወይም የኢንተርኔት ችግር ለሚገጥማቸው በዚህ ልጥፍ ውስጥ የተካተተውን የማመልከቻ ቅጽ በመሙላት በፖ.ሳ.ቁጥር 25534 አዲስ አበባ እንድትልኩ እንገልጻለን፡፡ ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0973078111 ወይም 0911106490 መደወል ይቻላል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ


   የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

 

በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ አመራር ዝግጅት ምልመላና ስምሪት ሥርዓት ማስተባበሪያ መመሪያ መሠረት ዶ/ር ሙሉነህ ለማ ወ/ሰማያት የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል፡፡