አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከቀድሞው የደቡብ ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ባደረገው የማዕድን አለኝታ ጥናት በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ ከ950 ሚሊየን ቶን በላይ የብረት እንዲሁም 429 ሚሊየን ቶን የድንጋይ ከሰል ማዕድን ከምችት መኖሩ ተረጋግጧል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ "Jhpiego" ጃፓይጎ ከተሰኘ መንግሥታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር በኮሌጁ በ“e-learning” የአካዳሚክ ሥራዎችን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር በሚያስችል የኦንላይን መተግበሪያ ፕላትፎርም አጠቃቀምና አተገባበር ላይ ልምድ ለማካፈል የተዘጋጀ የአንድ ቀን ወርክሾፕ ጥር 3/2016 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

8ው ዙር የማኅበረሰብ ጉድኝት ቀን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሁኔታ ጥር 6/2016 ዓ/ም ተከብሮ ውሏል፡፡ በዕለቱም ዩኒቨርሲቲው በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው የሚገኙ የተፈጥሮና የቱሪስት መስህብ ጸጋዎችን የሚያንጸባርቅ፣ ለከተማው ውበት ከፍ ያለ አበርክቶ ያለውና በ17.2 ሚሊየን ብር በከተማው መግቢያ ላይ ያስገነባውን አደባባይ ያስመረቀ ሲሆን የከተማው ማዘጋጃ ቤትና ማኅበረሰቡ አደባባዩ በጥንቃቄ እንዲያዝ በጋራ እንዲሠሩ ማሳሳቢያ ተሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የእናቶችንና ሕፃናትን ጤና ለማሻሻል በሚተገበረው ‹‹AMU-IUC›› ፕሮጀክት III ሥር ከሚከናወኑ ምርምሮች አንዱ የሆነውንና በጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ በነፍሰጡር እናቶችና ሕፃናት ጤና ሁኔታ ላይ በቪዲዮ የተመሠረተ የጤና ትምህርት የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ለማወቅ የተደረገውን የሙከራ ጥናት ውጤት ለማኅበረሰቡ ለማስተዋወቅ ጥር 04/2016 ዓ/ም በጊዶሌ ከተማ ወርክሾፕ ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡