- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከቀድሞው የደቡብ ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ባደረገው የማዕድን አለኝታ ጥናት በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ ከ950 ሚሊየን ቶን በላይ የብረት እንዲሁም 429 ሚሊየን ቶን የድንጋይ ከሰል ማዕድን ከምችት መኖሩ ተረጋግጧል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ ከ950 ሚሊየን ቶን በላይ የብረት ማዕድን ከምችት መኖሩ በጥናት ተረጋገጠ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ "Jhpiego" ጃፓይጎ ከተሰኘ መንግሥታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር በኮሌጁ በ“e-learning” የአካዳሚክ ሥራዎችን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር በሚያስችል የኦንላይን መተግበሪያ ፕላትፎርም አጠቃቀምና አተገባበር ላይ ልምድ ለማካፈል የተዘጋጀ የአንድ ቀን ወርክሾፕ ጥር 3/2016 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአርባ ምጭ ከተማ መግቢያ ላይ በ17.2 ሚሊየን ብር ያስገነባውን አደባባይ ጥር 6/2016 ዓ/ም በማስመረቅ ለአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር አስረክቧል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአርባ ምንጭ ከተማ ላይ በ17.2 ሚሊየን ብር ያስገነባውን አደባባይ በ8ኛው የማኅበረሰብ ጉድኝት ቀን አስመረቀ
- Details
8ኛው ዙር የማኅበረሰብ ጉድኝት ቀን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሁኔታ ጥር 6/2016 ዓ/ም ተከብሮ ውሏል፡፡ በዕለቱም ዩኒቨርሲቲው በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው የሚገኙ የተፈጥሮና የቱሪስት መስህብ ጸጋዎችን የሚያንጸባርቅ፣ ለከተማው ውበት ከፍ ያለ አበርክቶ ያለውና በ17.2 ሚሊየን ብር በከተማው መግቢያ ላይ ያስገነባውን አደባባይ ያስመረቀ ሲሆን የከተማው ማዘጋጃ ቤትና ማኅበረሰቡ አደባባዩ በጥንቃቄ እንዲያዝ በጋራ እንዲሠሩ ማሳሳቢያ ተሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: 8ኛው ዙር የማኅበረሰብ ጉድኝት ቀን በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ
- Details
የእናቶችንና ሕፃናትን ጤና ለማሻሻል በሚተገበረው ‹‹AMU-IUC›› ፕሮጀክት III ሥር ከሚከናወኑ ምርምሮች አንዱ የሆነውንና በጋርዱላ ዞን ዲራሼ ወረዳ በነፍሰጡር እናቶችና ሕፃናት ጤና ሁኔታ ላይ በቪዲዮ የተመሠረተ የጤና ትምህርት የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ለማወቅ የተደረገውን የሙከራ ጥናት ውጤት ለማኅበረሰቡ ለማስተዋወቅ ጥር 04/2016 ዓ/ም በጊዶሌ ከተማ ወርክሾፕ ተካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: በቪዲዮ የተመሠረተ የጤና ትምህርት በእናቶችና ጨቅላ ሕፃናት ጤና ላይ በጎ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር በጥናት ተገለጸ