ላለፉት 2 ዓመታት በ5 ክልሎች በሚገኙ 62 ወረዳዎች የሴፍቲኔት ተረጂ አርሶ አደሮችን ማዕከል በማድረግ ሲሠራ የቆየው የቤኔፊት ሪያላይዝ ፕሮግራም ሥራዎችን ዩኒቨርሲቲዎችና ሌሎች የመንግሥት አካላት በራስ አቅም ማስቀጠል እንዳለባቸው ከየካቲት 19-20/2013 ዓ/ም ሀዋሳ ላይ በተደረገው የፕሮግራሙ ክልላዊ የአፈፃፀም ግምገማ መድረክ ላይ ተገልጿል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

AMU has commemorated the 125th anniversary of iconic Adwa Victory with great zeal and fervor at Main Campus on 2nd March, 2021. Many war veterans with pips and gongs, Gamo elders draped in colorful ethnic attire, Gamo Zone officials, guests from different walks of life and AMU community graced the event. Click here to see the pictures

Arba Minch University in association with Ethiopian Public Health Institute (EPHI) has organized a 2-day workshop on multi-sectoral inter-disciplinary research findings on moringa stenopetala at New Hall, Main Campus, from 26th to 27th February, 2021. The 1st day saw presentation of 9 research findings that generated a much-needed synergy where researchers, academicians, officials and different stakeholders could discuss the multiple medicinal, epidemiological, biochemical and health benefits of moringa for the society. Click here to see the pictures

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቤኔፊት ሪያላይዝ (BENEFIT-REALISE) ፕሮግራም የ2 ዓመታት ዞናዊ አፈፃፀሙ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ለመወያየት የካቲት 16/2013 ዓ/ም ወርክሾፕ አዘጋጅቷል፡፡ ፕሮግራሙ ሊጠናቀቅ ጥቂት ጊዜያት የቀሩት በመሆኑ መልካም ተሞክሮዎችን በዘላቂነት ለማስፋፋት ከባለድርሻ አካላቱ የሚጠበቁ ሥራዎችና ኃላፊነቶች በመድረኩ በሰፊው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በሥሩ 6 ፕሮጀክቶችን ይዞ ላለፉት 5 ዓመታት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና አካባቢው ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን ሲሠራ የቆየው IUC ፕሮግራም በገለልተኛ አካላት በተደረገ የአፈፃፀም ግምገማ የላቀ ውጤት በማስመዝገቡ የ2ኛ ዙር የ5 ዓመት ዕድል ማግኘቱ ተገልጿል፡፡

የፕሮግራሙ ኃላፊ ዶ/ር ፋሲል እሸቱ እንደገለጹት IUC ፕሮግራም በሁለት ዙር የተከፈለ የ10 ዓመት ቆይታ ያለው ሲሆን 2ኛው ዙር ዕድል የሚወሰነው በመጀመሪያው ዙር በሚመዘገበው ውጤት ነው፡፡ በዚህም መሠረት ላለፉት ዓመታት የተማሪዎችን ውጤታማነት፣ የፋይናንስና የአፈፃፀም ሪፖርቶችንና ሌሎችም ሥራዎችን በለጋሽ አካሉ ተመርጦ የመጣው ገለልተኛ ገምጋሚ ቡድን በአካል በመገኘት ባደረገው የአፈፃፀም ግምገማ ፕሮግራሙ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ በመቻሉ 2ኛ ዙር ዕድል ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል፡፡