ላለፉት ሦስት ዓመታት እየጣለ ባለው ዝናብ አማካኝነት እየገባ ባለው ከፍተኛ ደለል ምክንያት የዓባያና ጫሞ ሐይቆች ከመጠን በላይ መሙላታቸውና ከብዙ ዓመታት በኋላ ሐይቆቹ ዳግም መገናኘታቸው ተገልጿል፡፡ ላለፉት 45 ዓመታት ተቋርጦ የቆየው ጫሞ በሰገን በኩል የሚያደርገው ፍሰትም ጥቅምት 16/2013 ዓ/ም ዳግም ጀምሯል፡፡

የ2013 የትምህርት ዘመን፡-

1. የምዝገባ ቀናት - ከጥቅምት 18-20/2013 ዓ.ም

2. የምዝገባ ቦታ - በካምፓስ ሬጅስትራር ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች

3. ትምህርት የሚጀመርበት ቀን ጥቅምት 23/2013 ዓ.ም መሆኑን እንገልጻለን፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

በ2012 ዓ/ም በኮቪድ - 19 ወረርሽኝ ምክንያት የተቋረጠው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማር ሂደት በ2013 የትምህርት ዘመን እንዲቀጥል መንግሥት በወሰነው መሠረት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ2012 ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎችን ከጥቅም 25 – 26/2013 ዓ/ም የመልሶ ቅበላ መርሃ ግብር ያካሂዳል፡፡

የኤፌዴሪ ፕሬዝደንት ክብርት አምባሳደር ሣህለወርቅ ዘውዴ ጥቅምት 12/2013 ዓ/ም አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተገኙበት ዩኒቨርሲቲው ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ካላቸው ቤተሰቦች የሚመጡ የ1ኛ ዓመት ተማሪዎች የትምህርት ድጋፍ እንዲያገኙ ከተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ከግብርና ሳይንስ ኮሌጅ እንዲሁም ከብራይት ፊውቸር አግሪካልቸር /BFA/ የደቡብ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ‹‹የሥርዓተ ፆታ ግንዛቤ፣ አካታች ጽንሰ ሀሳቦችና ዘዴዎቹ›› በሚል መሪ ቃል በሥራ ክፍሉ ለሚገኙ ባለሙያዎች እና ከተለያዩ ተቋማት ለተወጣጡ ባለድርሻ አካላት ከጥቅምት 09/2013 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 5 ቀናት ስሲጥ የነበረው የአሠልጣኞች ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ