አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢንስቲትዩት፣ አሜሪካ ሀገር የሚገኘው አላባስተር ኢንተርናሽናል/Alabaster International እንዲሁም ኬንያ የሚገኙት ገርል ቻይልድ ኔትወርክ/ Girl Child Network እና ጆሞ ኬንያታ የግብርናና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ/ Jomo Kenyatta University of Agriculture and Technology በመተባበር ‹‹Enset Cultivation, Development and Utilization in Ethiopia and Kenya›› በሚል ርእስ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመው የጀመሩት ዓለም አቀፍ የምርምር ትብብር ፕሮጀክት እየተተገበረ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ እ.ኤ.አ. ጥር 01, 2023 ተጀምሮ ለሦስት ዓመታት የሚቆየው ፕሮጀክት ከአንድ መቶ ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ በጀት የተመደበለት ሲሆን በዋናነት በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና በ‹‹Jomo Kenyatta University of Agriculture and Technology›› የሚተገበርና በ‹‹Alabaster International›› እና ‹‹Girl Child Network›› በገንዘብ የሚደገፍ ነው፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ክርስቲያን ኤይድ/Christian Aid/ እና ኤስኦኤስ ሳህል ኢትዮጵያ /SOS Sahel Ethiopia/ ከተሰኙ ግብረ ሠናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ከጋሞና ወላይታ ዞኖች ለተወጣጡ ማኅበራት ተወካዮችና ሥራ አጥ ወጣቶች ከጥር 29/2016 - የካቲት 15/2016 ዓ/ም በሁለት ዙሮች ከእንሰት ቃጫ እሴት የተጨመረባቸው ቁሳቁሶችን የሚያስችል ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

‹‹Computing and Software Engineering›› ፋከልቲ በ‹‹Artificial Intelligence(AI)›› እና ‹‹Large Language Models(LLMs)›› ዙሪያ ለመምህራንና ለቅድመና ድኅረ ምረቃ ተማሪዎች የካቲት 15/2016 ዓ/ም ሴሚናር አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በሒሳብ ት/ክፍል በ‹‹Numerical Analysis›› ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ወንድማገኘሁ ስምዖን የካቲት 26/2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ የ3 ዲግሪ ማጠናቀቂያ የምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት በዓባያ ካምፓስ አዲሱ የአስተዳደር ሕንፃ ላይ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ያቀርባል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ማዕከል ከዩኒቨርሲቲው የእንግሊዝኛ ቋንቋ ት/ክፍል እና ከአሜሪካ ኤምባሲ ጋር በመተባበር በጫሞ ካምፓስ ለሚገኙ 2ና 3 ዓመት የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ‹‹Social-Emotional Learning Program›› በሚል ርእስ ከየካቲት 17/2016 ዓ/ም ጀምሮ የ120 ሰዓታት ሥልጠና እየሰጠ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ