ማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ በ“ELT”፣ በ“Environment and Natural Resources Management” እና በ“Disaster Risk Management” ትምህርት ፕሮግራሞች በ3ኛ ዲግሪ ያሠለጠናቸውን ተማሪዎች ነገ ቅዳሜ ሰኔ/4/2014 ዓ/ም፣ የፊታችን ሰኞና ማክሰኞ ማለትም ሰኔ 6 እና 7/2014 ዓ/ም የመጨረሻ የምርምር ሥራቸውን የውጪና የሀገር ውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች በተገኙበት የሚያቀርቡ ይሆናል፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ-ምረቃ ት/ቤት አስተባባሪነት በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት የ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን አጠናቀው ለተመረቁ መምህራን 3ኛው የእንኳን ደኅና መጣችሁ ‹‹የዶክተሮች ቀን/Doctoral Day›› መርሃ-ግብር ግንቦት 30/2014 ዓ/ም ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ስር በሚገኙ ሦስት ፋከልቲዎች የቀረቡ 7 የድኅረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞች ግንቦት 29/2014 ዓ/ም የውጭ የሥርዓተ ትምህርት ግምገማ ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት ት/ክፍል ከአርባ ምንጭ መምህራን ማሠልጠኛ ትምህርት ኮሌጅ ጋር በመተባበር ለኮሌጁ የአስተዳደር ሠራተኞች በየሥራ ጠባያቸው በመከፋፈል ከግንቦት 23-26/14 ዓ/ም በተቋማዊ ባህርይ ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከጋሞ ዞን አካባቢ ጥበቃና ልማት ጽ/ቤት፣ ከአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደርና ከGIZ-CLM /ጂ.አይ.ዘድ-ሲኤል.ኤም/ ጋር በመተባበር በዓለም ለ49ኛ በሀገራችን ለ29ኛ ጊዜ የተከበረውን የዓለም የአካባቢ ቀን ‹‹አንድ ምድር ብቻ! - ከተፈጥሮ ጋር በዘላቂነት ተስማምቶ መኖር!›› በሚል መሪ ቃል ግንቦት 27/2014 ዓ.ም አርባ ምንጭና አካባቢዋን በማጽዳት፣ ችግኝ በመትከልና በቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ በደማቅ ሁኔታ አክብሯል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ