የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የኮምፒውቲንግ እና የሶፍትዌር ኢንጂነሪንግ ፋከልቲ የ3ኛ ዲግሪ ተማሪና የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መምህር አስቻለው አረጋ ‹‹Cloud-Enabled Smart and Green Healthcare Information Service Model›› በሚል ርዕስ በጤና ተቋማት ላይ ያሉ አገልግሎቶችን ለማዘመን ያቀረቡት የምርምር ንድፈ ሃሳብ ግንቦት 23/2014 ዓ/ም ተገምግሟል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የእንሰት ምርትና ምርታማነትን እንዲሁም የማብላላት ሂደትን የሚያሻሽሉ ቴክኖሎጂዎችን በጋሞ ዞን ደጋማ አካባቢዎች በሚገኙ 4 ወረዳዎች ለሚኖሩ እንሰት አብቃይ አርሶ አደሮች ለማዳረስ 2.3 ሚሊየን ብር የተመደበለት ፕሮጀክት ቀርጾ እየሠራ መሆኑን ገልጿል፡፡

በአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂና ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች አዘጋጅነት በኢንስቲትዩቶቹ የተለያዩ ሥራ ክፍሎች ለሚሠሩ ባለሙያዎች ከግንቦት 18-23/2014 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ 

በአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ‹‹የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ለዘላቂ ልማት እና ተግዳሮቶች/3rd National Conference on Innovation and Challenges in Engineering and Technology for Sustainable Development›› በሚል ርዕስ 3ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ዓውደ ጥናት ከግንቦት 26 - 27/2014 ዓ/ም ድረስ በደማቅ ሁኔታ ይካሄዳል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት/AWTI/ ከኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት/EWTI/ ጋር በመተባበር ለኢንስቲትዩቱ መምህራን፣ ተመራማሪዎችና ተማሪዎች በውሃ ንጽሕና አጠባበቅና በፍሳሽ አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ከግንቦት 19-21/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ