የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በደቡብ ክልል ከሚገኙ የተለያዩ ሆስፒታሎች ለተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች፣ የኦፕሬሽን ክፍል ነርሶች፣ አንስቴዥያ ባለሙያዎችና የሕክምና ዶክተሮች ከግንቦት 19-21/2014 ዓ/ም ‹‹ሰላማዊ የኦፕሬሽን ክፍልና የተሻለ የማገገም ሂደት/Safe Operating Room (OR) and Enhanced Recovery after Surgery Training›› በሚል ርዕስ ሀገር አቀፍ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ማኅበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ አስተባባሪነት በማሕፀንና ጽንስ ስፔሻሊስት ዶ/ር ነጋ ጩፋሞ የተመራ የሕክምና ቡድን በገረሴ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በመገኘት ለ4 አቅመ ደካማ እናቶች ነፃ የማሕፀን ውልቃት/መንሸራተት ቀዶ ጥገና ሕክምና አገልግሎት ግንቦት 19/2014 ዓ/ም ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹Christian Aid››/ክርስቲያን ኤይድ/ ከተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር የእንሰት አመራረትና ማብላላት ሂደትን ለማዘመን የሚረዱ በዩኒቨርሲቲው የተፈጠሩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ለማዳረስ 3.2 ሚሊየን ብር የተመደበለት ፕሮጀክት በትብብር እየሠሩ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የፕሮጀክቱን የሥራ እንቅስቃሴና አፈፃፀም አስመልክቶ ከድርጅቱ የመጣ ቡድን ግንቦት 16/2014 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ምልከታ አድርጓል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ለጫሞ ካምፓስ አዲስ ገቢ ሴት ተማሪዎች አቀባበልና የላቀ ውጤት ላመጡ የ3ኛ ዓመት ሴት ተማሪዎች የሽልማት መርሃ ግብር ግንቦት 11/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ 

ከታኅሣሥ 08/2014 ዓ/ም ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኅብረት ፓርላማ ምርጫ ግንቦት 14/2014 ዓ/ም አፈ-ጉባኤና ም/አፈ-ጉባኤ በመምረጥ ተጠናቋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ