የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረትና የሰላም ፎረም ከዩኒቨርሲቲው ጋር በመተባበር በ2014 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርሲቲው ለተቀላቀሉ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ከግንቦት 1-2 /2014 ዓ/ም አቀባበል አድርገዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግና ምቹ የገበያ ዕድል እንዲያገኙ ለማድረግ በተመሠረተው ዓለም አቀፍ ድርጅት ‹‹Vita›› ስር በኬኒያ ሀገር የተቋቋሙት የ‹‹Dream Team›› አባላት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለተቋቋሙት አቻ የ‹‹Dream Team›› አባላት፣ ለግብርና ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች ከሚያዝያ 24-26/2014 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ‹‹PlantVillage›› እና ‹‹PlantVillageNuru›› ሶፍትዌር መተግበሪያ (Software Application) አጠቃቀም ዙሪያ በንድፈ ሃሳብና በተግባር የተደገፈ ሥልጠና ሰጥተዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥራ ፈጠራ ልማትና ማበልጸጊያ ማዕከል በሥራ ፈጠራ አመለካከትና በመሠረታዊ የሥራ ፈጠራ ክሂሎት ዙሪያ ሚያዝያ 29/2014 ዓ/ም የመጀመሪያ ዙር ሥልጠና ለዓባያ፣ ጫሞ፣ ኩልፎ፣ ነጭ ሳርና ዋናው ግቢ ተመራቂ ተማሪዎች ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የሥራ ፈጠራ ማበልጸጊያ ማዕከል ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ጀረኔ ሥልጠናው ለተመራቂ ተማሪዎች በሥራ ፈጠራ ክሂሎት ላይ በቂ ግንዛቤ በማስጨበጥ ተመራቂዎች የተለያዩ አማራጮችን ተመልክተው ራሳቸውንና ሌሎችን መጥቀም የሚያስችል አቅም ይፈጥርላቸዋል ብለዋል፡፡

ራስን ማወቅ ለሥራ ፈጠራ ቀዳሚ ተግባር ሊሆን ይገባል ያሉት አሠልጣኝ መ/ርት አስቴር ሰይፉ ሥልጠናው ተማሪዎቹ ለሥራ ፈጠራ፣ ለራሳቸው እና ለሌላው ሰው ያላቸው አመለካከት መልካም አንዲሆን በማድረግ ተቀጣሪ ሳይሆኑ ቀጣሪ በመሆን ለቀጣይ ትውልድ የሥራ ፈጠራ እድልን እንዲያመቻቹ የሚረዳ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አሠልጣኝ መ/ር አሰግድ አጥናፉ በበኩላቸው ሠልጣኞች የአመለካከት ለውጥ እንዲያመጡ፣ እችላለሁ የሚለውን ስሜት አዳብረው በመነቃቃት ወደ ሥራ እንዲገቡና ውጤታማ እንዲሆኑ ይጠበቃል ብለዋል፡፡ የጊዜና የሀብት አጠቃቀም፣ የዕቅድ አዘገጃጀትና ተያያዥ ጉዳዮች  ላይ ግንዛቤን በመፍጠር ተማሪዎቹ ዕውቀት እንዲጨብጡ መደረጉን አሠልጣኙ አብራርተዋል፡፡

ሠልጣኝ ተማሪዎች ከሥልጠናው ያገኘነው ዕውቀት ለቀጣይ ሥራችን አጋዥና ለሥራ በር የሚከፍትልን በመሆኑ ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ እንዲሁም ሥራ በመፈለግ ጊዜያችንን ከማጥፋት የሚታደገን ነው ብለዋል፡፡

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቪታ/Vita/ ከተሰኘ መንግሥታዊ ካልሆነ ድርጅት የተሻሻሉና ማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎችን በጋሞ ዞን ለሚገኙ ማኅበረሰቦች ለማዳረስ በሚሠራው ፕሮጀክት ዙሪያ በጋራ ለመሥራት ሚያዝያ 28/2014 ዓ/ም ለ5 ዓመታት የሚቆይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ሊግ እና ከአርባ ምንጭ ከተማ ወጣቶች ሊግ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በከተማው ስድስት ቀበሌያት ውስጥ ከሚገኙ 12 ቀጠናዎች ለተወጣጡ 66 አመራሮችና 80 የአርባ ምንጭ ከተማ ወጣቶች አደረጃጀት አባላት ሚያዝያ 27/2014 ዓ/ም የአመራርነት ክሂሎት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ