የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ለባልታ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ለመማር ማስተማር ሥራ የሚውሉ የባዮሎጂ፣ የኬሚስትሪና የፊዚክስ ቤተ-ሙከራ ኬሚካሎችና ቁሳቁሶችን ሚያዝያ 8/2014 ዓ/ም ድጋፍ አድርጓል፡፡ ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን 130,000 (አንድ መቶ ሠላሳ ሺህ) ብር የሚያወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የአርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ መምህር፣ ታዋቂ የፈጠራ ባለቤትና በIBM ካምፓኒ ውስጥ ተመራማሪ ከሆኑት ቺፍ አርክቴክት ዶ/ር ኮሚ ወ/ማርያም ጋር አርቲፊሻል ኢንተሊጀንስን በዘላቂ የምግብ ዋስትናና ግብርናን በማዘመን ዘዴ በመጠቀም ላይ ሚያዝያ 7/2014 ዓ/ም ኦንላይን ሴሚናር አካሂዷል፡፡

በአዲሱ የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎች ኅብረት ፓርላማ ምርጫ መመሪያ መሠረት በ2012 ዓ.ም የተመረጠው የተማሪዎች ኅብረት ፓርላማ ሁለት ዓመት የሥራ ዘመን መጠናቀቁን ተከትሎ በአዲስ አባላት ለመተካት ከታኅሣሥ 8/2014 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የነበረው የዋና ሥራ አስፈፃሚ ምርጫ ሂደት ሚያዝያ 02/2014 ዓ.ም ተጠናቋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሰላም ፎረም አባላትና የ2014 ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎች ‹‹በፍቅር በመደመር ሰላማችንን እንጠብቅ›› እና ‹‹100 ቀናችንን በጽዳት ዘመቻና ችግኞችን ውሃ በማጠጣት እናሳልፍ›› በሚሉ መሪ ቃሎች በዋናው ግቢ የጽዳት ዘመቻና ችግኝ ውሃ የማጠጣት መርሃ-ግብር አካሂደዋል፡፡